Thursday, December 5, 2013

ወላጆች ስለ ትምህርትቤታችን ምን ይላሉ?

ኖቬምበር 3 2013 በተጠራው የወላጆች እና መምህራንን የምክክር ስብሰባ ላይ 41 ወላጆች እና መምህራን እንዲሁም የደብሩ አስተዳደር ተገኝተው ነበር፡፡ በዕለቱ በአዳጊዎች ትምህርት ቤቱ እንቅስቃሴዎች፤ ጥንካሬዎች እና ድክመቶች ውይይት ተደርጓል፡፡

ከውይይቱ በተጨማሪ ግን ወላጆች ስማቸውን ሳይገልጹ እንዲመልሱት የተዘጋጀ መጠይቅ ተሰጥቷቸው ነበር፡፡ መጠይቁ 17 ጥያቄዎች ያሉት ሲሆን የጥያቄዎቹም ይዘት በተማሪ ልጆች፤ በመምህራን፤ በወላጆች ጥረት፤ በትምህርት ቤቱ የወደፊት ተስፋ፤ እና የገንዘብ ክፍያን ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ነበሩ፡፡ (የታደለውን መጠይቅ ለማየት ይህንን ይጫኑ)

ወላጆች በመጠይቁ ወረቀት ላይ ያሰፈሩት መልሶች ሲጠቃለሉ በአብዛኛው በጎ እና ደጋፊ አመለካከት እንዳላቸው ሲያመለክት፤ አሉታዊ መልስ የሰጡባቸው ጥያቄዎች ለወደፊቱ በትምህርት ቤቱ ጥራት ላይ ማሻሻያ ለማድረግ የሚረዱ ጥቆማዎች ሆነው ተገኝተዋል፡፡ (የተጠናቀረውን የወላጆችመልስ እና ውጤት ለማየት ይህንን ይጫኑ)፡፡  ውጤቱም ለወላጆች በቤት አድራሻቸው ተልኳል፡፡

Sunday, December 1, 2013

የልምድ ልውውጥ ሪፖርት

በናዖድ ቤተሥላሴ
በደብራችን በደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን (3010 Earl Pl NE Washington, DC 20018) የሚገኘውንም የአዳጊዎች ትምህርት ክፍል ለማጠናከር እየተደረጉ ካሉ ዘርፈ ብዙ እንቅስቃሴዎች ውስጥ አንዱ የሌሎች እህት አብያተ ክርስቲያናትን ልምድ እና አሰራር ልምድ መቅሰም ነው፡፡
 
እሁድ ዲሴምበር 02 2013 በደብረ ገነት መድኃኒአለም ቤተክርስቲያን (4401 Old Branch Avenue  Temple Hills, MD 20748) ተገኝቼ፤ የአዳጊ ልጆች እና ወጣቶች ትምህርት አሰጣጥን ለመጎብኘት፤ ከልምዳቸውም ብዙ ለመማር ችያለሁ፡፡ ያገኘሁትንም መሰረታዊ ትምህርት፤ ጠቃሚ ልምድ እና ምክር በአጭሩ እነሆ፡-

·         ትምህርት ቤቱ፡- መስራታቸው በግልጽ የሚታይ  የቦርድ ተወካይ፤ የሃይማኖት መምህር እና የትምህረት ኮሚቴዎች አሉት

o   ለልጆች ትምህርት ቤት ብቻ የሚውል ብዙ ክፍሎች ያሉ አንድ ሙሉ ቤት ገዝተዋል

o   በደብሩ የታወቀ እና የተፈቀደ በፈንድ ሬዚንግ አድርገው በተለያየ ጊዜ 30 ሺ እና 40 ሺ ዶላር አሰባስበዋል

o   በደብሩ ሥር ያለ፤ የታወቀ የባንክ አካውንት አለው

o   የተጻፈ መተዳደሪያ ደንብ፤ የተሳለ አስተዳደራዊ መዋቅር፤ በቂ የማስተማርያ ቦታ አለው

o   በቋሚነት፤ ለልጆች ትምህርት ቤት የተቀጠረ የሃይማኖት መምህር (ካህን) አለው

o   እስከ 200 የሚደርሱ መደበኛ ተማሪዎች አሉ

o   የተጻፈ የቋንቋ ካሪኩለም/ሳምንታዊ ትምህርቶች/ አሉት

o   36 ቋሚ ነገር ግን በጎፈቃደኛ መምህራን አሉት

o   ወላጆች ተራ ወጥቶላቸው በየሳምንቱ መምህራንን ወይም ልጆቹን ይረዳሉ

o   የአካዳሚ ቱተር አገልግሎት ይሰጣል

o   ለውጤታማ ተማሪዎች ስኮላርሺፕ ይሰጣል

·         ተማሪዎች

o   ሦስት ምድብ አላቸው

§  ዕድሜ 5-7(ጀማሪ ደረጃ)     --ዕድሜ 8-12(መካከለኛ ደረጃ)  --ዕድሜ 13-18(የመጨረሻ ደረጃ)

o   የትምህርት ሰዓታቸው 7፡45-11፡00 ነው

o   በወር አንድ እሁድ ቅዳሴ እንዲያስቀድሱ ይደረጋል

o   የሚማሩት አማርኛ ቋንቋ፤ ሃይማኖት፤ እና ግብረ ዲቁና ነው

o   ዓመታዊ የምርቃት እና የጌት ቱጌዘር ዝግጅቶች አላቸው

·         መምህራን

o   በአንድ ክፍል 5 መምህራን ያስተምራሉ

o   አንድ መምህር አንድ ክብ ጠረጴዛ ይይዛል፤ በዕለቱ፤ በየጠረጴዛው በአማካይ ከ4-5 ተማሪዎች አይቻለሁ፡፡

o   በዕለቱ የሚያስተምሩት ትምህርት; በትምህረት ክፍሉ ተዘጋጅቶ ይሰጣቸዋል

o   የክፍል ፈተና ያርማሉ፤ ፈተና ይሰጣሉ፤

o   በቀጥታ ከወላጆች ጋር አይደራደሩም፡፡ የወላጆችን ኮሚቴ የወላጆችን  ጉዳይ ይይዝላቸዋል፡፡

·         የተማሪ ወላጆች

o   የደብሩ አባል መሆን አለባቸው

o   ክፍያ ይከፍላሉ (ለስናክ፤ ለአልባሳት፤ ለስቴሽነሪ የሚሆን)

§  በቤተሰብ፡- ለ1 ልጅ 10 ዶላር፤ ለ2 ልጅ 15 ዶላር፤ ለ3 ልጅ 20 ዶላር

o   የወላጆች አስተባባሪዎች አሉ

o   የወላጆች አለግልግሎት መመሪያ ማኑዋል ይሰጣቸዋል

o   ወላጆች በወር አንድ ጊዜ የሚያገለግሉበት መርሀግብር ይወጣላቸዋል

o   በስልክ፤ በኢሜይል፤ በአካል፤ በቤተክርስቲያን መድረክ ላይ ማሳሰቢያ እና ጥሪ ይደረግላቸዋል

o   በየሳምንቱ 15 ወላጆች (በየክፍሉ 5) ይመደባሉ

·         ኮሚቴዎች

o   ያነጋገርኳቸው አራት አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት ናቸው

o   ያየኃቸው ግልጽ የሥራ ኃላፊነትያላቸው እና እርስ በእርሳቸው ደስ የሚል መግባባት ያላቸው ናቸው፡፡

o   ነባር እና የአገልግሎቶ ዓላማቸውን የሚያውቁ ስለሆኑ የአገልግሎቱን ውስጥና ውጪ፤ ድክመት እና ጥንካሬ ለይተው ያውቃሉ

o   በዲያስፖራ ወላጆች ውስጥ ያለ የልጅ አስተዳደግ ፓራዶክዶክስ እና የልጆች ማንነት ቀውስ ችግር በጥልቅ የተረዱ ስለሆኑ የትምህርት ቤቱን እንቅስቃሴ ይህንን ማኅራዊ ችግር በመፍታት ዙርያ እንዲቃኝ እየሞከሩ ነው፡፡

o   የሰጡኝ አክብሮት፤ ትምህርት እና ምክር የማይረሳ ነው፡፡

·         የስኬት መላዎች

o   ከወላጆች ጋር አንድ- ለአንድ ግብብነት መፍጠር

o   ደንቦችን ወላጆች እንዲያረቁ መጋበዝ፤ ከዚያ ማስፈጸም፤ ማስከበር፤ መሞከር

o   አገልግሎቱን በተገኘው አጋጣሚ እና መንገድ ሁሉ ማስተዋወቅ

o   ልጆች ቤተክርስቲያን ውስጥ ችሎታቸውን የሚያሳዩበት መድረክ (መነባንብ፤ ድራማ ወዘተ..) መፍጠር

o   ስኮላር ሺፕ፤ ሽልማት... መፍጠር
Measure of Success
  • Because of the kids school, the number of Church members increased by 30%
  • 100% of the kids that have passed through the school system are now in college
  • Those college kids (especially those who won the church's scholarship) serve back their church in their field of profession and preference.
  • Above all, the school is a proud source of well mannered, socially stable and academically competent citizens for the community.

The committee (ዶ/ር ሶሎሞን ገብሩ: ቢኒያም ገብረወልድ: ሐና ተስፋዬ: ቤተልሔም ዘውዴ: ) express their willingness to continue sharing their experience and resources as needed.

Friday, September 20, 2013

እንቁጣጣሽ መዝሙር


የደብሩ አዳጊ ልጆች ለ2006ዓ.ም መቀበያ እንቁጣጣሽ መዝሙር ሲያቀርቡ


Saturday, August 17, 2013

Enqoqelesh /Riddle /: One way to improve our kids language skills

By Mekdim T.

If you grew up in Ethiopia, you most definitely enjoyed playing “Enqoqelesh”. As children we not only learned new words playing “Enqoqelesh”, but we have also practiced how forming short but meaningful sentence and improved our grammar. As parents raising our children abroad, we face many challenges especially when it comes to teaching our kids Amharic. Well how about “Enqoqelesh”? How nice would it be to challenge your kids to use the little Amharic they know to form a clever hint or solve a riddle or an “Enqoqelesh”. “Enqoqelesh” is a nice game to play and interact with our kids while developing their Amharic vocabulary and grammar.

The most common “Enqoqelesh” that would come, at least for me is the one about BAKELA or black eyed pea and it goes like this.
Player 1 - “Enqoqelesh”
Player 2 – “Men Awkilish?” ( What do I know?)
Player 1 – “Ayenuan Tekukula Gebeya Yemitweta?” (One that goes to market with eye liner make up on?)
Player 2 – “BAKELA!” ( Black eyed pea!)

If player 2 did not know the answer he should give/ name a country for player 1 and player 1 replies like as follows.
Player 2 – Addis Baba’n Setichehalehu. (I give you Addis Ababa.)
Player 1 – Addis Ababa gebeche tedesch Melsu Bakela new. (I would be happy to go to Addis Ababa! The answer is Black eyed pea)


Another Enqoqelesh
Player 1 - “Enqoqelesh”
Player 2 – “Men Awkilish?” ( What do I know?)
Player 1 – “Tseguruan Abetira Gebeya Yemitweta?” (One that goes to market with with combed hair?)
Player 2 – “SUFF!” ( Sunflower Seed!)

Sure these Enqoqeleshs may make no sense in English as they would in Amharic and the cultural context. However, we can create suitable Enqoqeleshs that our children can understand and enjoy. An example would be:
Player 1 - “Enqoqelesh”
Player 2 – “Men Awkilish?” ( What do I know?)
Player 1 –Aba hulun ye emisalemut. (What Aba to bless us with?)
Player 2 – “MESQEL!” ( the cross!)

So what do you think? Are you going to try some of your own Amharic riddles with your kids? Please feel free to share with us your creative Enqoqleshes. 
Write your Enkoklish below by clicking comment

Monday, August 5, 2013

የላይብረሪ አገልግሎት ጅምር

ለአዳጊ ልጆች ትምህርት እና ዕድገት የሚሆኑ ጥቂት የቋንቋ እና ሃይማኖት መማርያ መጽሐፍት፤ እና ቁሳቁሶች በአዳጊዎች ትምህርት ክፍል ይገኛሉ፡፡ ያሉትን የላይብረሪ ሀብቶች ለመጠቀም፤ የሚመጡትንም ለማስተዳደር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የምትሰጠው ወ/ሮ ወይንሸት ናት፡፡
 
በቀጣይ ሳምንታት ውስጥም ለወላጆች ስለ ላይብሪው አጠቃቀም መሠረታዊ ሕጎች የሚገልጽ ደብዳቤ የሚላክላቸው ሲሆን፤ ወላጆች ላይብረሪውን ለመጠቀምም ሆነ ለማጠናከር ማድረግ ስለሚፈልጉት እገዛ እና ልገሳ፤ ወ/ሮ ወይንእሽትን እንዲያነጋግሩ እንጠይቃለን፡፡

Sunday, July 21, 2013

ተማሪዎች ጥያቄ ጠይቁ ሲባሉ…

የመሠረተ ሃይማኖት ክፍል ተማሪዎች፤ ዛሬ ስለተማሩት ትምህርት ብቻ ሳይሆን፤ በጠቅላላ በሃይማኖት ዙርያ መልስ ማግኘት ያቃታቸውን ጥያቄዎች እንዲጠይቁ እድል ተሰጣቸው፡፡  ልጆቹም የተሰጣቸውን እድል አላባከኑም፤ ሁሉም ወረቀት እና ብዕሩን አገናኝቶ፤ ጥያቄ መጻፍ ጀመሩ፡፡ በእጅ የጻፉትን ማየት ከፈለጋችሁ ይህንን ተጫኑ፡፡


የጠየቁትም ጥያቄ እነሆ … I post the Questions asked by the kids As Is!
 

1.      When you die where do you go?    (ላ. አ)

2.      If God created the world, who created him? Why do church names start with ቤተ?   (S.)

3.      To go to heaven, do you need to believe only or do you have follow the Ten Commandments too? (A. M.)

4.      In one of the scripture readings of the New Testaments, Jesus as a boy was bored. So with clay he made a living Pigeon. Later people decided to cut that part of the scripture out. Why did they do that Knowing this was second time of Creation?   (U. S)

5.      How come there aren’t any girl preists? (L.)

6.      Why can’t we wash after ቁርባን? Why did people hate Jesus? Why did God tell Jonah to go to ነነዌ?   (B.H.)

7.      Is there such thing as Reincarnation of souls?   (H.Y.)

8.      Do the pries wear the cloth they wear a church always? (B.)

9.      What is Jesus name in Amharic? (D. H.)

10.  Was Satan an angel?  If Satan was a angel what was his name before? Why do the priests wear the gowns? (B.G.)  

11.  Why can’t girls pour holly water in a cup and handle it like boys do? Why can’t you eat or drink before you take the holy flesh and blood? (M. S.)

12.  Has any body seen God other than in Dreams? Are we all related since we came from Adam and Eve? (B.T.)

 የልጅን ጥያቄ፤ ልጅ በሚገባው መንገድ መመለስ ግድ ነውና፤ እኛም መምህራን ጠይቀን ያገኘነውን መልስ ከጥያቄዎቹ ቀጥሎ እንለጥፋለን፡፡ወደፊት፡፡

Sunday, July 7, 2013

የሁለተኛ ሩብ ዓመት ፈተናዎች

ዛሬ ተማሪዎች የሁለተኛ ሩብ ዓመት የቋንቋ እና የሃይማኖት ፈተናዎችን ወስደዋል፡፡
ዛሬ በተለያየ ምክንያት ፈተናውን ሊቀበሉ ላልቻሉ ተማሪዎች፤ ፈተናዎቹ ከዚህ በታች ባሉት ሊንኮች ላይ ተቀምጠዋል፡፡

የመሠረተ ሃይማኖት ተማሪዎችን
የዓምደ ሃይማኖት ተማሪዎች ፈተና አልተሰጠም
ፈተናው የመምህራኑን ጥረት ውጤት እና የተማሪዎቹን የእውቀት ደረጃ ለመለካት ቢሆንም፤ በተዛማጅ ግን  በፈተናው የሚገኘውን ውጤት መሰረት በማድረግ፤ ተመጣጣኝ ችሎታ ያላቸውን ተማሪዎች በአንድ አይነት ክፍል ለማቀፍ ለሚደረገው አዲስ የክፍል ምደባ የሚረዳ ነው፡፡

Sunday, June 30, 2013

አደራ ‹‹ቅዳሴ ተማሩ››

ጓዝ ጠቆሎ፤ ከዋሽንግተን ዲ.ሲ ወደ አትላንታ መሄድ በራሱ ከባድ ቢሆንም፤ ለመምህር የሻነው ግን በጣም የከበደው፤ በሃይማኖት ኮትኩቶ ያሳደጋቸው ተማሪዎቹን ትቶ መሄድ ነው፡፡ ስለዚህም፤ ዛሬ በደብሩ የአዳጊዎች ትምህርት ክፍል በተደረገለት መጠነኛ የሽኝት ስጦታ ስነስርዓት ላይ፤ መምህር የሻነው ያደረገው ስጦታችንን መቀበል ብቻ አይደለም፤ ላስተማራቸው ተማሪዎች፤ የውዳሴ ማርያም የጸሎት መጽሐፍ ስጦታ እና የ ‹‹ቅዳሴ ተማሩ›› አደራም በመስጠትም እንጂ፡፡

የፊደል ቤት የ2013 ሁለተኛ ሩብ አመት ፈተና

 የፊደል ቤት የ2013 ሁለተኛ ሩብ አመት ፈተና በ ጁን 30, 2013 እና በ ጁላይ 7, 2013 ይሰጣል፡፡ የፈተናውን ይዘት ለመመልከት ይህንን ይጫኑ፡፡

Tuesday, June 25, 2013

የመዝሙር ጥናት መርሐግብር

አዳጊ ልጆች ኦርቶዶክሳዊ መዝሙራትን የሚያጠኑበት፤ ከቤተክርስቲያን የመዝሙር መሳሪያዎች፤ ሥርዓት እና ባህል ጋር የሚተዋወቁበት የትምህርት መርሐ ግብር ተዘጋጅቶላቸዋል፡፡ የአራቱ ክፍል ተማሪዎች፤ በየሳምንቱ፤ በተራ በተራ፤ በቤተክርስቲያን ውስጥ ለምዕመናን መዝሙር እንዲያቀርቡ ማስቻል የመርሐግብሩ ተጨማሪ ግብ ነው፡፡
የመዝሙ ጥናት መርሐግብሩ የሚካሄደው፤  በበጎ ፈቃደኛ የሰንበት ትምህርት መዘምራንን መምህርነት ሲሆን፤ ትምህርቱ አዳጊዎች በመደበኛነት ከሚማሩት የሃይማኖት ትምህርት ጋር ተያይዞ የሚሰጥ ሥልጠና ይሆናል፡፡
የመዝሙር ጥናት ወርኃዊ መርሐግብር፤ በዚህ ድረ ገጽ ላይ በተዘጋጀው የመዝሙር መርሐግብር ገጽ() ላይ ይለጠፋል፡፡ እንደ አስፈላጊነቱም፤ ሙሉ የመዝሙራት ስንኞች ይለጠፋሉ፡፡

Sunday, June 23, 2013

በኪነ ጥበቡ አየለ

ይህ ድንቅ ልጅ የሚሰራቸውን የእደ ጥበብ ውጤቶች የሚያይ ሰው በሁለት ነገር ይገረማል፤ 1ኛ. ልጁ በሚሰራቸው የእደ ጥበብ ስራዎች ጥራት 2ኛ. በልጁ የመጠሪያ ስም እና ግብር መጣጣም፡፡
ስሙ በኪነ ጥበቡ አየለ ይባላል፡፡ በደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርርስቲያን የመሠረተ ሃይማኖት ክፍል ተማሪ ነው፡፡ በኪነ ጥበቡ ካለው ጨዋ ስነምግባር እና የቤተክርስቲያን ፍቅር በተጨማሪ፤ ኢትዬጵያዊ ባሕሉን እና ታሪኩን የሚያንጸባርቁ የእደ ጥበብ ስራዎችን ይሰራል፡፡
በኪነጥበቡ አየለ ከጥበብ ሥራዎቹ ጋር
በኪነጥበቡ አየለ እና ዘማሪ የሻነው መኮንን
ከአሁን በፊት የቅዱስ ላሊበላን ሕንጻ ሞዴል ሰርቶ ያሳየው ይህ አዳጊ፤ ዛሬ ደግሞ በቤተክርስቲያናችን እና በኢትዬጵያዊ ባህላችን ውስጥ ትልቅ ቦታ ያለውን የሙዚቃ መሳሪያ ክራር ሞዴል ሰርቶ አሳይቷል፡፡

በፎቶግራፉ ላይ እንደምታዩት፤ የሰራው ሞዴል፤ ‹‹የልጅ ሥራ›› አይመስልም፡፡ በቅርጹ ተመጣጣኝነት፤ በክሮቹ አደራደር እና አቆጣጠር ረቂቅነት፤ በሞዴሉ ጥንካሬ እና ሞዴሉን ለመስራት በተጠቀመባቸው ጥሬ እቃዎች እንደሚንጻባረቀው፤ የኪነጥበቡ ሥራ የጥበበኛ ሥራ ነው፡፡
 በፎቶግራፉ ላይ የሚታየው፤ ኪነ ጥበቡ አየለ፤ በቤተክርስቲያን ውስጥ ሃይማኖት እና ባሕል ከሚያስተምረው መምህሩ፤ ዘማሪ የሻነው መኮንን ጋር የተነሳውን ፎቶ ነው፡፡

የኪነ ጥበቡን ሥራዎችን መነሻ በማድረግ፤ የደብሩ አዳጊዎች ክፍል፤ ወደፊት፤  በአዳጊዎች የተሰሩ ተመሳሳይ የእደ ጥበብ እና ፈጠራ ውጤቶችን ለምዕመናን የሚያሳይበት፤ ለሌሎች ልጆችም ማስተማርያ የሚያውልበት መላ እንደሚፈልግ ይጠበቃል፡፡

Monday, June 17, 2013

የመምህራን እና አስተባባሪዎች ጠቅላላ ውይይት

የአዳጊዎች ትምህርት ክፍል መምህራን እና አስተባባሪዎች፤ እሁድ ጁን 16 2013 ጠቅላላ ውይይት አድርገው ነበር፡፡ በውይይቱም የተሳተፉት አባላት ብዛት 12 ሲሆኑ፤ የተወያዩበት እና ያስተላለፉትም ውሳኔዎች ከሞላ ጎደል ይህንን የመስላሉ፡፡


1. የተዘጋጀውን ካሪኩለም ከልጆቹ አቅም/ ደረጃ/ ጋር ማጣጣምን በተመለከተ፡፡

በየክፍሉ ያሉ ተማሪዎች የቋንቋ እውቀት እና የእድሜ ደረጃ የተዘበራረቀ ስለሆነ፤ የተዘጋጀውን ካሪኩለም ለመተግበር እንቅፋት ሆኗል፡፡ ህይንን ለማስተካከል ሁለት ደረጃዎቸ ያሉት መፍትሔ ታስቧል፡፡
  •  ደረጃ አንድ፡፡ የሁለተኛው ሩብ ዓመት ፈተና ከተሰጠ በኋላ፤ ለፊደል ቤት፤ ንባብ ቤት ፤ እና መሠረተ ሃይማኖት ተማሪዎች አዲስ አይነት የክፍል ድልድል ማድረግ፡፡ይህም በተማሪዎች የቋንቋ እውቀት ላይ የተመሰረተ ድልድል ስለሚሆን፤ በአንድ ክፍል ውስጥ ተመጣጣች ችሎታ/ደረጃ/ ያላቸውን ልጆች ለማግኘት ይረዳል፡፡ ወላጆች ይህንን አስቀድመው እንዲያውቁትም ማስታወቂያ ደብዳቤ ተልኳል፡፡
  • ደረጃ ሁለት፡፡ በዓመቱ መጨረሻ ላይ፤ ካሪኩለሙ ለተማሪዎች ይመጥናል አይመጥንም የሚል ምዘና አድርጎ፤ የካሪኩለም ክለሳ ማካሄድ
2. የቴክስት ቡክ ዝግጅትን በተመለከተ

የአዳጊዎች ትምህርት ክፍል ተማሪዎች የሚማሩበት፤ መምህራንም የሚያስተምሩበት ቋሚ ማስተማርያ መጽሐፍ/ ቴክስት ቡክ/ የለም፡፡ በሚቀጥለው የትምህርት ዘመን፤ የሚከተሉት ቴክስቶች እንዲዘጋጁ፤ ታስክ ፎርስ ተቋቁሟል፡፡
  • ቋንቋ ማስተማርያ ቴክስተ ቡክ፡፡ ይህንን እንዲያዘጋጁ የተመደቡት የታክስ ፎርሱ አባላት አቶ መኮንን፤ አቶ ካሰኝ፤ አቶ ናዖድ እና ወ/ሮ እመቤት ናቸው፡፡
  • የሃይማኖት ማስተማርያ ቴክስት ቡክ፡፡ ይህንን እንዲያዘጋጁ የተመደቡት የታክስ ፎርሱ አባላት፤ አቶ ዳንኤል፤ አቶ የሻነው እና አቶ ሰሎሎሞን ናቸው፡፡
ማሳሰቢያ፡፡ የሚዘጋጀት ማስተማርያዎች ጥቅም ላይ የሚውሉት፤ ለቤተክርስቲያን ቦርድ ቀርበው ከታረሙ እና ከተፈቀዱ ብቻ ነው፡፡

3. የአዳጊዎች መዘምራን በተመለከተ

  • በትምህርት ክፍሉ የታቀፉት ከ150 በላይ የሚሆኑ አዳጊ ልጆች፤ በየሳምንቱ እሁድ ከቅደሴ በኋላ መዝሙር የመያቀርቡበት መርሐ ግብር ተነድፏል፡፡ ይህንን ለማድረግ፤ ልጆቹ በየክፍላቸው የሚያጠኑት መዝሙር እና የሚያቀርቡ መዝሙር ዝርዝር እቅድ ተዘጋጅቶ፤ በቅርቡ በዚህ ድረ ገጽ ላይ ይለጠፋል፡፡
4. የቤተሰብ ቀን በዓል ዝግጅት

  • ተማሪዎች፤ ወላጆች እና መምህራን የሚተዋወቁበት እና የሚመካከሩበት አጋጣሚዎችን ማብዛት አስፈላጊ መሆኑ ስለታመነበት፤ በሚቀጥሉት ወራት ውስጥ የቤተሰብ በዓል ቀን ተወስኖ፤ ልጆች ከወላጆቻው ጋር የሚታደሙበት፤ እየተዝናኑ የሚመካከሩበት መርሐግብር ይዘጋጃል፡፡ ይህም መርሐግብር በአቶ ቢኒያም እና በአቶ መሠረት አስተባባሪነት ይከናወናል፡፡
5. የሰንበት ት/ቤት አባላት እና ወላጆ ለአዳጊ ልጆች ክፍል የሚሰጡት ድጋፍ ከአቅም በታች መሆኑን በተመለከተ እንዲሁም

6. የዓምደ ሃይማኖት ክፍል የመማር ማስተማር ሂደት ያሉበትን ውስብስብ ችግሮች በተመለከተ ጥልቅ ውይይይት ተደርጎባቸዋል፡፡

Sunday, May 12, 2013

ለተማሪዎች አዲስ የክፍል ድልድል የማድረግ ዕቅድ

ለወላጆች የተላከ ማሳሰቢያ ደብዳቤ፡

በደብራችን የአዳጊዎች ትምህርት ቤት ውስጥ የሚማሩ 150 መደበኛ እና ከ50 በላይ ኢ-መደበኛ ተማሪዎች አሉ፡፡ ሁሉም ተማሪዎች የሚማሩበት ተመጣጣኝ ዓመታዊ ሥርዓተ ትምህርት እና 15 በጎ ፈቃደኛ አስተማሪዎች አላቸው፡፡ አዳጊዎቹ በመሰረታዊነት የሚማሩትም አማርኛ ቋንቋ፤ ሃይማኖት እና ግብረ ገብ ነው፡፡

በየሩብ ዓመቱም፤ የተማሪዎቹን የመማር ደረጃ የሚለካ እና የመምህራኑን የማስተማር ዘዴ ውጤታማነት የሚለካ ፈተና ይሰጣል፡፡ የመጀመርያው ሩብ ዓመት ፈተናም ማርች 31 2013 ተሰጥጧል፡፡

የዚህ ሩብ ዓመት የተማሪዎች የፈተና ውጤት በግልጽ እንደሚያሳየው ከሆነ፤ ጥቂት የማይባሉ ተማሪዎች ለተመደቡበት ክፍል የሚመጥን ደረጃ ላይ አይደሉም፡፡ ውጤታቸው፤ አብረዋቸው ከሚማሩ ሌሎች ተማሪዎች አንጻር ሲታይ እጅግ በጣም ዝቅተኛ ወይም እጅግ በጣም ከፍተኛ ነው፡፡

የልጅዎን ደረጃ ለማወቅ፤ እባክዎ፤ የልጅዎ ውጤት ሪፖርት ካርድ ጀርባ ላይ ያሉትን መረጃዎች ያንብቡ፡፡

የትምህርት አስተዳደሩም፤ የችግሩን ምክንያት በዝርዝር ለማየት ሞክሯል፡፡ ለችግሩ ምክንያት ከሆኑት መካከል ዋነኛው የወላጆች ክትትል እና ድጋፍ ማነስ ሲሆን፤ የመምህራን እጥረትም ሌላው ችግር ነው፡፡ ሌላው ቁልፍ ችግር ግን፤ ጥቂት የማይባሉ ልጆች፤ አሁን ለሚማሩበት ክፍል በዕድሜ ወይም በዕውቀት ደረጃ የማይመጥኑ መሆናቸው ነው፡፡

ስለዚህ፤ ተማሪዎች በቀጣዩ ሩብ ዓመት (ኤፕሪል እስከ ጁን) ውስጥ በሚያሳዩት መሻሻል መሰረት፤ ወደ አዲስ እና የሚመጥናቸው ክፍል ይደለደላሉ፡፡ የዚህ ማሳሰቢያም ዓላማ፤ ወላጆች ለደብራችን ትምህርት ቤት ጥራት እና ውጤታማነት ለምናደርገው ጥረት በጎ ድጋፋቸውን እና አስተያየታቸውን ከመስጠት በተጨማሪ፤ ተማሪ ልጆቻቸው የሚሰጣቸውን የክፍል ሥራ እና የቤት ሥራ በማሰራት እንዲረዱን ለማሳወቅ ነው፡፡

የአዳጊዎች ትምህርት ክፍል






Monday, April 29, 2013

የተማሪዎች ሪፖርት ካርድ አዘገጃጀት


መምህራን የሪፖርት ካርድ ለተማሪዎች የሚያዘጋጁበት ብዙ ጥሩ ዘዴ አላቸው፡፡ እንደ አማራጭ መላ የሚያገለግል ሌላም ቀላል ኮምፒውተራዊ ዘዴ አለ፡፡ ኮምፒውተር ለአገልግሎታችን መቀላጠፍ የሚረዱ፤ ብዙ መላዎች እንዳሉት ግልጽ ነው፡፡ ከእነዚህ መላዎች ውስጥ የሚከተሉትን ጥያቄዎቻችንን የሚመልስ ትምህርታዊ የሥልጠና ጽሑፍ ተዘጋጅቷል፡፡ የትምህርቱን ጥቅም ለመረዳት፤ የጥያቄዎቹን ክብደት መረዳት ይበጃል፡፡

ጥያቄ

1. ለ200 ተማሪዎች፤ ለእያንዳንዱ፤ በየትምህርት ዘርፉ ያገኙትን ነጥብ ለመጻፍ፤ እና ትክክለኛ ሪፖርት ካርድ ለማዘጋጀት፤ መምህራን ምን መላ ይጠቀማሉ?

2. ትምህርት ቤቱ፤ ለ1000 ምእመናን እና ወላጆች፤ የግል ደብዳቤ መላክ ቢያስፈልግ፤ እንዴት ይሰራዋል፡፡ ስማቸው ያልተሞላ 1000ሺ ደብዳቤ አባዝቶ፤ ከዚያ የ1000 ሰዎችን ስም በየደብዳቤው ይጽፋል? ወይስ…ለሚመለከተው ሁሉ ብሎ የጅምላ ደብዳቤ ያዘጋጃል?

እንዲህ ያሉ ስራዎች፤ ቀላል ቢሆኑም፤ አድካሚ እና ጊዜ ፈጂ የሚሆኑበት ጊዜ አለ፡፡ ብዙ ስህተትም ሊሰራ ይችላል፡፡



እኒህን ጥያቄዎች የሚመልስ የስልጠና ትምህርት ለማግኘት ይህንን ይጫኑ ወይም Resources በሚለው ገጽ ውስጥ ገብታችሁ፤ የሜይል መርጅ ሥልጠና How to Lesson የሚለውን ተጫኑ፡፡

Wednesday, April 24, 2013

Student Report Card Template

Over 150 Regular Student of Debere Meheret Kids Education Department will receive their First Quarter 2013 Report Card. 
To see the Report card template click here


Monday, April 1, 2013

የሩብ ዓመት ፈተና ተሰጠ

መምህራን የትምህርት ዘዴያቸውን ውጤታማነት የሚገመግሙበት፤ ወላጆች ልጆቻቸው መማር አለማማራቸውን የሚያረጋግጡበት አንዱ መንገድ ፈተና መስጠት ነው፡፡ የአዳጊዎች ትምህረት ክፍልም ማርች 31 ቀን 2013፤ በሥሩ ለሚማሩ ከ150 በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች የአንደኛ ሩብ ዓመት ፈተና ሰጠ፡፡
 
ፈተናው የአማርኛ ቋንቋ እና የሃይማኖታዊ እውቀትን ለመመዘን የተዘጋጀ ሲሆን፤ የተሰጠውም በሁለት አይነት መንገድ ነው፡፡ 1ኛ በክፍል ውስጥ ፈተና 2ኛ እቤት በሚወሰድ ፈተና፡፡
የክፍል ውስጥ ፈተናው፤ የቡድን እኛ የግል ጥያቄዎችን ያጠቃለለ ሲሆን፤ እያንዳንዱ ተማሪ ያለበትን ትክክለኛ የእውቀት ደረጃ ለመመዘን ይረዳል በሚል እሳቤ የተደረገ ነው፡፡ እቤት የሚወሰደው ፈተና ዋና አላማ፤ ወላጆች ልጆቻቸውን በማስተማር ያላቸውን ተሳትፎ ለመመዘን ሲሆን፤ ጥያቄዎቹ የተዘጋጁትም ተማሪዎቹ የወላጆቻቸውን እርዳታ ካላገኙ በቀር በግል ለመስራት እንዲቸገሩ ታስቦ ነው፡፡ ልጆቹ እቤት በወሰዱት ፈተና የሚያገኙት ውጤት፤ የወላጆቹ የድጋፍ መጠን መለኪያም የሚሆነው ለዚህ ነው፡፡
በሚቀጥሉት ሳምንታትም ውስጥ ሁለት ዋና ዋና ተግባራት እንደሚከናወኑ ይጠበቃል፡፡
  1. የተማሪዎችን ምዘና ውጤት ለወላጆች ማሳወቅ የመጀመርያው ሥራ ሲሆን፤ ለሁሉም ተማሪዎች ወጥ የሆነ ፎርማት ያለው የፈተና ሪፖርት ማድረጊያ ቅጽ እየተዘጋጀ ነው፡፡
  2.  
  3. መምህራኑ እና አስተባባሪዎች ፈተናውን በተመለከተ የጋራ ውይይት ያደርጋሉ፡፡ በውይይቱም፤ መምህራኑ የፈተናውን አዘገጃጀት እና አሰጣጥ ሥርዓት በተመለከተ ስኬቶችን እና ድክመቶችን መዝነው፤ ለወደፈቱ የሚጠቅሙ ማሻሻያ እና ማስተካከያ መላዎችን እንዲቀይሱ ይጠበቃል፡፡
 

Wednesday, March 20, 2013

የሚዲያ ክፍል አገልግሎቱን ሊጀምር ነው


ሚዲያ ክፍል፤ Print, Video, Audio, Web, ITን የሚያጠቃልል አገልግሎት ነው፡፡ የተቋቋመበት ዋና ዓላማ፤ አዳጊ ልጆች ሃይማኖታቸውን፤ ቋንቋቸውን እና ባህላቸውን በቴክኖሎጂካዊ መላ እንዲማሩ ማድረግ ሲሆን የአገልግሎቱ ፍሬም የሚለካው ለአዳጊዎች በሚያቀርበው ቴክኖሎጂካዊ አገልግሎት ነው፡፡ በተዛማጅም፤ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ፤ የሚዲያ ክፍል ለመምህራን፤ ለተማሪዎች ወላጆች እና ለካህናት የሙያ ድጋፍም ሊሰጥ ይችላል፡፡

የክፍሉን አገልግሎት ለመጀመር የሚያስችሉ ቁሳቁሶች በቤተክርስቲያኑ የተገዙ እና በበጎ አድራጊ ወላጆች የተለገሱ ሲሆን፤ ከመሳሪያዎቹም ጥቂቶቹ

1.  Laptop
2.  DLP Projector
3.  Printer (Laser Jet monochrome)
4.  Printer (Color)
5.  Overhead Projectors
ዋናዎቹ ናቸው፡፡
የሚዲያ ክፍል፤ አገልግሎቱን ለመጀመር በመምህራን እና በወላጆች የሚሞላ አጭር መጠይቅ ያዘጋጀ ሲሆን፤ የሚመለከታቸው ሁሉ መጠይቁን ሞልተው ለሚዲያ ክፍል ወይም ለአዳጊዎች ክፍል አስተባባሪዎች እንዲሰጡ ይጠበቃል፡፡ መጠይቁን ለማየት ይህንን ይጫኑ

Thursday, March 7, 2013

የመጀመርያ ሩብ ዓመት ፈተና ይሰጣል

News Report posted by Hanna

በዚህ በያዝነው ወር (ማርች 2013) መጨረሻ ሳምንት ላይ፤ በደብሩ የአዳጊዎች ትምህርት ክፍል ለሚማሩ ተማሪዎች በሙሉ የመጀመርያ ሩብ ዓመት ማጠቃለያ ፈተና ይሰጣል፡፡ ፈተናው የሚዘጋጀው በየክፍሉ በሚያስተምሩ መምህራን ሲሆን፤ ፈተናው ከሥርዓተ ትምህርቱ ይዘት ጋርመጣጣሙ ከተረጋገጠ በኋላ፤ ለተማሪዎች ይሰጣል፡፡

ፈተናው የሚሰጠው በሁለት መንገድ ነው፡፡ የመጀመርያው መንገድ፤ ተማሪዎች እዚያው ክፍል ውስጥ የሚጨርሱት የክፍል ፈተና ነው፡፡ ሁለተኛው መንገድ ደግሞ ተማሪዎች እቤት ወስደው ከወላጆቻቸው ጋር ይሚሰሩት፤ እቤት የሚወሰድ ፈተና ሲሆን ዓላማውም የወላጆችን ተሳትፎ ለመመዘን ነው፡፡

የፈተናው ይዘት፤ እንደ ተማሪዎቹ የክፍል ደረጃ ቢለያይም፤ ጥያቄዎቹ የሚያተኩሩት ግን በ ሁለት የትምርት ዘርፎች ላይ ይሆናል፡፡ 1ኛ. የአማርኛ ቋንቋ ማለትም (ፊደል፤ ንባብ፤ ጽሑፍ፤ ንግግር) 2ኛ. የሃይማኖት ትምህርት ማለትም (እምነት፤ ሥርዓት እና መዝሙር)

እንደተለመደው፤ ፈተና የሚሰጠው የተማሪዎችን እውቀት ለመመዘን ቢሆንም፤ በደብሩ የሚሰጠው ፈተና ግን ከዚህ በላይ ተጨማሪ ግቦች አሉት እነርሱም፡
 
  1. በትምህርት ቤቱ፤ ወጥ የሆነ እና የተቀናጀ የፈተና እና የምርቃት ሥርዓት ባሕል መጀመር
  2. የሥርዓተ ትምህርቱን ውጤታማነት መገምገም
  3. ወላጆች በማስተማር ሂደት ውስጥ ያላቸውን ተሳትፎ መመዘን ነው፡፡

የፈተናው ውጤት፤ ለተማሪዎቹ ወላጆች የሚላክ ሲሆን፤ የውጤት ማሳወቂያው የሚይዘው የተማሪዎቹን የፈተና ውጤት፤ የክፍል አቴንዳንስ እና የመምህራኑን አስተያየት ነው፡፡ ናሙናውን ለማየት ይህንን ይጫኑ፡፡

በሥርዓተ ትምህርቱ መሰረት፤ የሚቀጥሉት የሁለተኛው፤ የሦስተኛው፤ እና የአራተኛው ሩብ ዓመት መመዘኛ ፈተናዎች የሚሰጡት በ June, September and December ወራት መጨረሻ ሳምንታት ውስት ነው፡፡

 
 

Sunday, February 24, 2013

ለመምህራን የድረ ገጽ ማኔጅመንት ሥልጠና ተሰጠ

የአዳጊ ልጆች መምህራን በዛሬው ዕለት የድረ ገጽ ማኔጅመንት ሥልጠና ወስደዋል፡፡ ሥልጠናው የተዘጋጀው ‹‹ልጆቻችንን የሚገለግሉትን መምህራን እናገልግላቸው›› በሚል መርህ ሲሆን፤ በሥልጠናው ወቅት መምህራን ራሳቸውን ችለው፤ በዚህ ድረ ገጽ ላይ ጽሑፍ፤ ስዕል እና ቪዲዬ ማውጣት የሚችሉበትን ዘዴዎች ተምረዋል፤ ተለማምደዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በሚለጥፉት ትምህርቶች ውስጥ ደጋፊ የውስጥና የውጪ ሊንኮችን መፍጠር የሚችሉበትን መንገድ አይተዋል፡፡

ከግራ ወደ ቀኝ፡- ቢኒያም ዮሴፍ፤ ዳንኤል ኃይለመስቀል፤ ሰሎሞን ወርቁ፤ መኮንን አክሌ፤ ሐና ደጋ
ለሠልጣኞቹ የተሰጡ ሁለት መማርያ ወረቀቶች ነበሩ፡፡ 1ኛ፡-ለሥልጠናው ዕለት ተዘጋጅተው መምጣት ያለባቸውን ጉዳዬች የሚያብራራ ወረቀት ሲሆን  ሁለተኛው ደግሞ በስድስት ክፍለ ትምህርቶች የተከፋፈለ የትምህርት ወረቀት ነው፡፡ የትምህርት ወረቀቱን ለማየት ይህንን ይጫኑ፡፡

ይህንን የድረ ገጽ ማኔጅመንት ሞያ የቀሰሙት መምህራን፤ በሚቀጥሉት ወራት ውስጥ፤ በየክፍላቸው የሚያስተምሩትን ትምህርቶች፤ በዚህ ድረ ገጽ ዓምዶች ላይ መለጠፍ ይጀምራሉ፡፡  

ይሄ ሥልጠና፤ ለመምህራን ከሚሰጡ የሙያ ማሻሻያ ሥልጠናዎች አንዱ ሲሆን፤ ወደፊት በዚህ ስልጠና ላልተሳተፉ መምህራን እና አገልጋዬች፤ ሌሎች ተዛማጅ የኮምፒውተር እና የሥርዓተ ትምህርት አተገባበር ሥልጠናዎች ይሰጣሉ፡፡

Thursday, February 21, 2013

ማስታወቂያ

ባለፈው ሳምንት የንባብ ክፍል ተማሪዎች ከመደበኛዉ ስርኣተ ትምህርቱ ያላገኙትን ለማካካስ እንዲመች ተማሪዎች እስካሁን ያሉትን መልመጃዎች እንዲጨርሱ ወላጆች ይረዷችዉ ዘንድ በኣክብሮት እንጠይቃለን።
 
ከንባብ ክፍል

Thursday, February 14, 2013

የድረ-ገጽ ማኔጅመንት ሥልጠና ይሰጣል



የአዳጊ ልጆችን በማስተማር እና በማስተባበር ላይ ለሚገኙ መምህራን እና አገልጋዬች፤ የድረ-ገጽ ማኔጅመንት ሥልጠና ይሰጣል፡፡ የሥልጠናው ዓላማ፤ መምህራን እና አስተባባሪዎች፤ በዚህ ድረ ገጽ ላይ ሳምንታዊ ትምህርቶችን እና መልዕክቶችን እንዲለጥፉ ማስቻል ነው፡፡
ሥልጠናው ሊሰጥ የታቀደው እሁድ ጃንዋሪ 24፤ 2013፤ ከሥርዓተ ቅዳሴ በኋላ ባለው ሰዓት ሲሆን፤ ሥልጠናው በጠቅላላው 4 ሰዓታት ይፈጃል፡፡ የሥልጠናውም ዋና ይዘት፤ መምህራን በዚህ ድረ ገጽ (ብሎግ) ላይ ጽሑፍ፤ ስዕል እና ቪዲዬ የሚለጥፉበትን ቴክኒክ ማሳየት ሲሆን፤ በተዛማጅም፤  የድረ ገጹን የሚመለከቱ ጉዳዬች ላይ ሀሳብ እና አስተያየት ይሰበሰባል፡፡
በሥልጠናው ወቅት፤ እያንዳንዱ ሰልጣኝ፤ የራሱን ላፕቶፕ ኮምፒውተር የሚጠቀም ሲሆን፤ የስልጠናው አዘጋጆችም ለሰልጣኞች የተዘጋጁ የሥልጠና ወረቀቶችን ይሰጣሉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ፤ እያንዳንዱ ሠልጣኝ፤ የተዘጋጁ ትምህርታዊ ጽሑፎችን በድረ ገጾች ላይ በመለጠፍ፤ ተግባራዊ ልምምድ ያደርጋል፡፡
ይህ ሥልጠና፤ የአዳጊ ልጆች መምህራንን ቴክኒካዊ ብቃት ለመጨመር ከሚደረጉ ጥረቶች አንዱ ሲሆን፤ በቀጣይም ሌሎች የቡድን እና የግል ሥልጠናዎች ይደረጋሉ፡፡

Tuesday, January 22, 2013

The Future is already here!

ዘጋቢ፡-ብሥራተ ገብርኤል

የወላጆች ጥረት በቤተክርስቲያን ተቋማዊ ዝግጅት ካልተደገፈ፤ በአንጻሩም የቤተክርስቲያን ዝግጅት በወላጀቾች መንፈሳዊ እና ቤተሰባዊ ጥረት ካልታገዘ፤  ልጆቻችን የያዙትን ይለቃሉ፤ ሲከፋም ስደተኞችን ለሚያጠቃው የማንነት ቀውስ አደጋ ይጋለጣሉ...ወዘተ እያልኩ ስለ ስለቤተክርስቲያን ተቋማዊ ዝግጅት በድጋሚ እንዳስብ ያደረገኝ ይሄ ልጅ ነው፡፡

 
  
ቀኑ ቃና ዘገሊላ ነውና፤ Jan 20, 2013፤ ውጪ፤ በቤተክርስቲያኑ ዓውደ ምህረት ላይ፤ ታቦተ ህጉ እየነገሰ ነው፡፡ ካህናትም ያሬዳዊ ዜማ እና ሽብሸባ እያቀረቡ ነው፡፡ ይሄ ልጅ ደግሞ


blessing

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን፡፡.......In The Name of The Father, The Son and The Holy Spirit. Amen.

Amen

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ ወለ ወላዲቱ ድንግል፤ ወለ መስቀሉ ክቡር፤ አሜን::