Sunday, June 23, 2013

በኪነ ጥበቡ አየለ

ይህ ድንቅ ልጅ የሚሰራቸውን የእደ ጥበብ ውጤቶች የሚያይ ሰው በሁለት ነገር ይገረማል፤ 1ኛ. ልጁ በሚሰራቸው የእደ ጥበብ ስራዎች ጥራት 2ኛ. በልጁ የመጠሪያ ስም እና ግብር መጣጣም፡፡
ስሙ በኪነ ጥበቡ አየለ ይባላል፡፡ በደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርርስቲያን የመሠረተ ሃይማኖት ክፍል ተማሪ ነው፡፡ በኪነ ጥበቡ ካለው ጨዋ ስነምግባር እና የቤተክርስቲያን ፍቅር በተጨማሪ፤ ኢትዬጵያዊ ባሕሉን እና ታሪኩን የሚያንጸባርቁ የእደ ጥበብ ስራዎችን ይሰራል፡፡
በኪነጥበቡ አየለ ከጥበብ ሥራዎቹ ጋር
በኪነጥበቡ አየለ እና ዘማሪ የሻነው መኮንን
ከአሁን በፊት የቅዱስ ላሊበላን ሕንጻ ሞዴል ሰርቶ ያሳየው ይህ አዳጊ፤ ዛሬ ደግሞ በቤተክርስቲያናችን እና በኢትዬጵያዊ ባህላችን ውስጥ ትልቅ ቦታ ያለውን የሙዚቃ መሳሪያ ክራር ሞዴል ሰርቶ አሳይቷል፡፡

በፎቶግራፉ ላይ እንደምታዩት፤ የሰራው ሞዴል፤ ‹‹የልጅ ሥራ›› አይመስልም፡፡ በቅርጹ ተመጣጣኝነት፤ በክሮቹ አደራደር እና አቆጣጠር ረቂቅነት፤ በሞዴሉ ጥንካሬ እና ሞዴሉን ለመስራት በተጠቀመባቸው ጥሬ እቃዎች እንደሚንጻባረቀው፤ የኪነጥበቡ ሥራ የጥበበኛ ሥራ ነው፡፡
 በፎቶግራፉ ላይ የሚታየው፤ ኪነ ጥበቡ አየለ፤ በቤተክርስቲያን ውስጥ ሃይማኖት እና ባሕል ከሚያስተምረው መምህሩ፤ ዘማሪ የሻነው መኮንን ጋር የተነሳውን ፎቶ ነው፡፡

የኪነ ጥበቡን ሥራዎችን መነሻ በማድረግ፤ የደብሩ አዳጊዎች ክፍል፤ ወደፊት፤  በአዳጊዎች የተሰሩ ተመሳሳይ የእደ ጥበብ እና ፈጠራ ውጤቶችን ለምዕመናን የሚያሳይበት፤ ለሌሎች ልጆችም ማስተማርያ የሚያውልበት መላ እንደሚፈልግ ይጠበቃል፡፡

No comments:

Post a Comment

እናመሰግናለን፡፡ተሳትፎዎን ይቀጥሉ፡፡

blessing

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን፡፡.......In The Name of The Father, The Son and The Holy Spirit. Amen.

Amen

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ ወለ ወላዲቱ ድንግል፤ ወለ መስቀሉ ክቡር፤ አሜን::