Sunday, June 30, 2013

አደራ ‹‹ቅዳሴ ተማሩ››

ጓዝ ጠቆሎ፤ ከዋሽንግተን ዲ.ሲ ወደ አትላንታ መሄድ በራሱ ከባድ ቢሆንም፤ ለመምህር የሻነው ግን በጣም የከበደው፤ በሃይማኖት ኮትኩቶ ያሳደጋቸው ተማሪዎቹን ትቶ መሄድ ነው፡፡ ስለዚህም፤ ዛሬ በደብሩ የአዳጊዎች ትምህርት ክፍል በተደረገለት መጠነኛ የሽኝት ስጦታ ስነስርዓት ላይ፤ መምህር የሻነው ያደረገው ስጦታችንን መቀበል ብቻ አይደለም፤ ላስተማራቸው ተማሪዎች፤ የውዳሴ ማርያም የጸሎት መጽሐፍ ስጦታ እና የ ‹‹ቅዳሴ ተማሩ›› አደራም በመስጠትም እንጂ፡፡
 

በዚህ አጋጣሚም ወንድማችን፤ በሄደበት ሁሉ እግዚአብሔር እንዲጠብቀው፤ መንገዱ እንዲቃናለት እና የሚወደውንም የልጆ አገልግሎት በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥል ከልብ እንመኛለን፡፡


 
 
በስንብት ንግግሩም በድጋሚ እንዳረጋገጠልን፤ ወንድማችን በድረገጻችን ላይ ትምህርታዊ ቪዲዮዎችን እና ትምህርቶች በመለጠፍ፤ እንዲሁም ለተወጠነውን የማስተማርያ መጽሐፍ ዝግጅት የሚሆኑ ሀሳቦችን በመለገስ የተልዕኮ አገልግሎቱን ይሰጠናል፡፡ 
 
 

No comments:

Post a Comment

እናመሰግናለን፡፡ተሳትፎዎን ይቀጥሉ፡፡

blessing

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን፡፡.......In The Name of The Father, The Son and The Holy Spirit. Amen.

Amen

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ ወለ ወላዲቱ ድንግል፤ ወለ መስቀሉ ክቡር፤ አሜን::