Library

የመጽሐፍቱን ሙሉ ዝርዝር እና ስዕል ከዚህ ገጽ መጨረሻ ላይ ተቀምጧል (Scroll down)፡፡

ስለ ላይብረሪው….

·         የላይብረሪያኗ(ኑ) ኃላፊነቶች

a.     መጽሐፍትን እና ቁሳቁሶችን መዝግቦ በሥርዓት መዝግቦ ማስቀመጥ

b.     አዳዲስ መጽሐፍትን ለተማሪዎች እና ወላጆች ማስተዋወቅ

c.     ለወላጆሚዘጋጁ ትምህርታዊ መጽሔቶችን ማሰራጨት

d.     ለመምህራን እና ወላጆች ማዋስ

e.     የተዋሱ ሰዎች ዕቃዎችን በሰዓቱ እንዲመልሱ ማሳሰቢያ መላክ (ስልክ፤ኤሜይል፤ቴክስት)

f.      ለጠፉ እቃዎች የሚሰበሰቡ ክፍያዎችን ካሉ፤ በቤተክርስቲያን ገንዘብ ያዥ በኩል በደረሰኝ እንዲገቡ ማድረግ

·         መዋስ የሚችሉ እነማን ናቸው

a.    መምህራን

b.     መደበኛ ተማሪ እንደሆኑ የተረጋገጠላቸው ተማሪዎች

c.     ወላጆቻቸው የአገልግሎት ፎርም አጠናቀው የሞሉ

d.     የሚዋሱ ሰዎች ስልካቸውን ወይም ኢሜይላቸውን ማስመዝገብ ግዴታቸው ነው፡፡

·         የጊዜ ገደብ

a.     መጽሐፍት የሚዋሱት ለ1-2 ሳምንት ነው

b.     መምህራን ለተማሪዎቻቸው የሚሰጡት የተለየ የጊዜ ገደብ ካለም ተቀባይነት አለው

·         የጠፉ፤ የተሰበሩ፤ የተበላሹ ዕቃዎች

a.     የተዋሱ ሰዎች፤ የተዋሱት ዕቃ ቢጠፋባቸው ምትኩን መግዛት ወይም መግዣ ገንዘቡን መክፈል አለባቸው

·         ልገሳ

a.     ለልጆች ቋንቋ እና ሃይማኖ ማስተማርያ የሚጠቅሙ መጽሐፍትን እና ዕቃዎችን ለመለገስ ያሰበ ሰው፤ ዕቃዎቹን ከማምጣቱ በፊት ላይብረሪኗን (ወ/ሮ የወይንሸትን) ወይም አስተባባሪዎችን አግኝቶ ናሙናውን ማሳየት አለበት፡፡

·         የላይብረሪ ቦታ

a.     ላይብረሪው በማስተባባሪያ ጽሕፈት ቤት ውስጥ ይገኛል

b.     የሚሰጠውን አገልግሎት የማዋስ አገልግሎት ብቻ ነው (ልዩ የማንበቢያ ቦታ የለውም)




    ርዕስ
    ደራሲ/አዘጋጅ/ተርጓሚ
    ለማዳው  አንኮ እና
    አለም እሸቱ
    ምርጥ የኤዞፕና የግሪክ ተረቶች
    አለም እሸቱ
    ቀበጧ ውሮ
    አለም እሸቱ
    ተንኮለኛው ዱዱ እና
    አለም እሸቱ
    ትንሹ አንበሳ እና
    አለም እሸቱ
    አያ ጅቦ እና ጎረቤቶቹ
    አለም እሸቱ
    እንቁልልጭ እና
    አለም እሸቱ
    ካሳሁንና ብርቅዬዎቹ የዱር እንስሳት
    አለም እሸቱ
    ከልጆች ወደ ልጆች
    ዜና ማርቆስ እንዳለው
    ዘመናዊ የአማርኛ መጽሐፍ-1
    አዲሱ ያለው
    ዘመናዊ የአማርኛ መጽሐፍ-2
    አዲሱ ያለው
    ብላቴና የልጆች ግጥም
    እምሻው ገ/ዮሐንስ
    ቁልጭ
    ተስፋዬ ገብረማርያም ኃይሉ
    የሕፃናት ዓለም
    እስክንድር ስዩም ዮሐንስ
    ቹቹ በጎዳና
    ዳንኤል ነጋሽ
    የዲባዲ ተረት (ኤሊና ጥንቸል)
    ሳምራዊት አርአያ መርሻ
    ዶክተር ጥንቸል እና..
    አንዳርጌ መስፍን
    ንብሊስ የመልካም ልጆች ምግባር መጽሐፍ
    ገብረክርስቶስ ኃይለሥላሴ
    እና ተስፋዬ ጥበቡ አብርሃም
    አማርኛ አጋዥ 1ኛ ክፍል
    ጌትነት ማሞ እና
    የኃላሸት ደሳለኝ
    የትንሷ ልጅ ህልም
    ግርማ አለማየሁ እና
    ብርሃኑ ለማ

    1 comment:

    እናመሰግናለን፡፡ተሳትፎዎን ይቀጥሉ፡፡

    blessing

    በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን፡፡.......In The Name of The Father, The Son and The Holy Spirit. Amen.

    Amen

    ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ ወለ ወላዲቱ ድንግል፤ ወለ መስቀሉ ክቡር፤ አሜን::