Wednesday, March 20, 2013

የሚዲያ ክፍል አገልግሎቱን ሊጀምር ነው


ሚዲያ ክፍል፤ Print, Video, Audio, Web, ITን የሚያጠቃልል አገልግሎት ነው፡፡ የተቋቋመበት ዋና ዓላማ፤ አዳጊ ልጆች ሃይማኖታቸውን፤ ቋንቋቸውን እና ባህላቸውን በቴክኖሎጂካዊ መላ እንዲማሩ ማድረግ ሲሆን የአገልግሎቱ ፍሬም የሚለካው ለአዳጊዎች በሚያቀርበው ቴክኖሎጂካዊ አገልግሎት ነው፡፡ በተዛማጅም፤ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ፤ የሚዲያ ክፍል ለመምህራን፤ ለተማሪዎች ወላጆች እና ለካህናት የሙያ ድጋፍም ሊሰጥ ይችላል፡፡

የክፍሉን አገልግሎት ለመጀመር የሚያስችሉ ቁሳቁሶች በቤተክርስቲያኑ የተገዙ እና በበጎ አድራጊ ወላጆች የተለገሱ ሲሆን፤ ከመሳሪያዎቹም ጥቂቶቹ

1.  Laptop
2.  DLP Projector
3.  Printer (Laser Jet monochrome)
4.  Printer (Color)
5.  Overhead Projectors
ዋናዎቹ ናቸው፡፡
የሚዲያ ክፍል፤ አገልግሎቱን ለመጀመር በመምህራን እና በወላጆች የሚሞላ አጭር መጠይቅ ያዘጋጀ ሲሆን፤ የሚመለከታቸው ሁሉ መጠይቁን ሞልተው ለሚዲያ ክፍል ወይም ለአዳጊዎች ክፍል አስተባባሪዎች እንዲሰጡ ይጠበቃል፡፡ መጠይቁን ለማየት ይህንን ይጫኑ

No comments:

Post a Comment

እናመሰግናለን፡፡ተሳትፎዎን ይቀጥሉ፡፡

blessing

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን፡፡.......In The Name of The Father, The Son and The Holy Spirit. Amen.

Amen

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ ወለ ወላዲቱ ድንግል፤ ወለ መስቀሉ ክቡር፤ አሜን::