Sunday, February 24, 2013

ለመምህራን የድረ ገጽ ማኔጅመንት ሥልጠና ተሰጠ

የአዳጊ ልጆች መምህራን በዛሬው ዕለት የድረ ገጽ ማኔጅመንት ሥልጠና ወስደዋል፡፡ ሥልጠናው የተዘጋጀው ‹‹ልጆቻችንን የሚገለግሉትን መምህራን እናገልግላቸው›› በሚል መርህ ሲሆን፤ በሥልጠናው ወቅት መምህራን ራሳቸውን ችለው፤ በዚህ ድረ ገጽ ላይ ጽሑፍ፤ ስዕል እና ቪዲዬ ማውጣት የሚችሉበትን ዘዴዎች ተምረዋል፤ ተለማምደዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በሚለጥፉት ትምህርቶች ውስጥ ደጋፊ የውስጥና የውጪ ሊንኮችን መፍጠር የሚችሉበትን መንገድ አይተዋል፡፡

ከግራ ወደ ቀኝ፡- ቢኒያም ዮሴፍ፤ ዳንኤል ኃይለመስቀል፤ ሰሎሞን ወርቁ፤ መኮንን አክሌ፤ ሐና ደጋ
ለሠልጣኞቹ የተሰጡ ሁለት መማርያ ወረቀቶች ነበሩ፡፡ 1ኛ፡-ለሥልጠናው ዕለት ተዘጋጅተው መምጣት ያለባቸውን ጉዳዬች የሚያብራራ ወረቀት ሲሆን  ሁለተኛው ደግሞ በስድስት ክፍለ ትምህርቶች የተከፋፈለ የትምህርት ወረቀት ነው፡፡ የትምህርት ወረቀቱን ለማየት ይህንን ይጫኑ፡፡

ይህንን የድረ ገጽ ማኔጅመንት ሞያ የቀሰሙት መምህራን፤ በሚቀጥሉት ወራት ውስጥ፤ በየክፍላቸው የሚያስተምሩትን ትምህርቶች፤ በዚህ ድረ ገጽ ዓምዶች ላይ መለጠፍ ይጀምራሉ፡፡  

ይሄ ሥልጠና፤ ለመምህራን ከሚሰጡ የሙያ ማሻሻያ ሥልጠናዎች አንዱ ሲሆን፤ ወደፊት በዚህ ስልጠና ላልተሳተፉ መምህራን እና አገልጋዬች፤ ሌሎች ተዛማጅ የኮምፒውተር እና የሥርዓተ ትምህርት አተገባበር ሥልጠናዎች ይሰጣሉ፡፡

No comments:

Post a Comment

እናመሰግናለን፡፡ተሳትፎዎን ይቀጥሉ፡፡

blessing

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን፡፡.......In The Name of The Father, The Son and The Holy Spirit. Amen.

Amen

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ ወለ ወላዲቱ ድንግል፤ ወለ መስቀሉ ክቡር፤ አሜን::