Thursday, December 5, 2013

ወላጆች ስለ ትምህርትቤታችን ምን ይላሉ?

ኖቬምበር 3 2013 በተጠራው የወላጆች እና መምህራንን የምክክር ስብሰባ ላይ 41 ወላጆች እና መምህራን እንዲሁም የደብሩ አስተዳደር ተገኝተው ነበር፡፡ በዕለቱ በአዳጊዎች ትምህርት ቤቱ እንቅስቃሴዎች፤ ጥንካሬዎች እና ድክመቶች ውይይት ተደርጓል፡፡

ከውይይቱ በተጨማሪ ግን ወላጆች ስማቸውን ሳይገልጹ እንዲመልሱት የተዘጋጀ መጠይቅ ተሰጥቷቸው ነበር፡፡ መጠይቁ 17 ጥያቄዎች ያሉት ሲሆን የጥያቄዎቹም ይዘት በተማሪ ልጆች፤ በመምህራን፤ በወላጆች ጥረት፤ በትምህርት ቤቱ የወደፊት ተስፋ፤ እና የገንዘብ ክፍያን ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ነበሩ፡፡ (የታደለውን መጠይቅ ለማየት ይህንን ይጫኑ)

ወላጆች በመጠይቁ ወረቀት ላይ ያሰፈሩት መልሶች ሲጠቃለሉ በአብዛኛው በጎ እና ደጋፊ አመለካከት እንዳላቸው ሲያመለክት፤ አሉታዊ መልስ የሰጡባቸው ጥያቄዎች ለወደፊቱ በትምህርት ቤቱ ጥራት ላይ ማሻሻያ ለማድረግ የሚረዱ ጥቆማዎች ሆነው ተገኝተዋል፡፡ (የተጠናቀረውን የወላጆችመልስ እና ውጤት ለማየት ይህንን ይጫኑ)፡፡  ውጤቱም ለወላጆች በቤት አድራሻቸው ተልኳል፡፡

No comments:

Post a Comment

እናመሰግናለን፡፡ተሳትፎዎን ይቀጥሉ፡፡

blessing

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን፡፡.......In The Name of The Father, The Son and The Holy Spirit. Amen.

Amen

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ ወለ ወላዲቱ ድንግል፤ ወለ መስቀሉ ክቡር፤ አሜን::