1. የተዘጋጀውን ካሪኩለም ከልጆቹ አቅም/ ደረጃ/ ጋር ማጣጣምን በተመለከተ፡፡
በየክፍሉ ያሉ ተማሪዎች የቋንቋ እውቀት እና የእድሜ ደረጃ የተዘበራረቀ ስለሆነ፤ የተዘጋጀውን ካሪኩለም ለመተግበር እንቅፋት ሆኗል፡፡ ህይንን ለማስተካከል ሁለት ደረጃዎቸ ያሉት መፍትሔ ታስቧል፡፡
- ደረጃ አንድ፡፡ የሁለተኛው ሩብ ዓመት ፈተና ከተሰጠ በኋላ፤ ለፊደል ቤት፤ ንባብ ቤት ፤ እና መሠረተ ሃይማኖት ተማሪዎች አዲስ አይነት የክፍል ድልድል ማድረግ፡፡ይህም በተማሪዎች የቋንቋ እውቀት ላይ የተመሰረተ ድልድል ስለሚሆን፤ በአንድ ክፍል ውስጥ ተመጣጣች ችሎታ/ደረጃ/ ያላቸውን ልጆች ለማግኘት ይረዳል፡፡ ወላጆች ይህንን አስቀድመው እንዲያውቁትም ማስታወቂያ ደብዳቤ ተልኳል፡፡
- ደረጃ ሁለት፡፡ በዓመቱ መጨረሻ ላይ፤ ካሪኩለሙ ለተማሪዎች ይመጥናል አይመጥንም የሚል ምዘና አድርጎ፤ የካሪኩለም ክለሳ ማካሄድ
የአዳጊዎች ትምህርት ክፍል ተማሪዎች የሚማሩበት፤ መምህራንም የሚያስተምሩበት ቋሚ ማስተማርያ መጽሐፍ/ ቴክስት ቡክ/ የለም፡፡ በሚቀጥለው የትምህርት ዘመን፤ የሚከተሉት ቴክስቶች እንዲዘጋጁ፤ ታስክ ፎርስ ተቋቁሟል፡፡
- ቋንቋ ማስተማርያ ቴክስተ ቡክ፡፡ ይህንን እንዲያዘጋጁ የተመደቡት የታክስ ፎርሱ አባላት አቶ መኮንን፤ አቶ ካሰኝ፤ አቶ ናዖድ እና ወ/ሮ እመቤት ናቸው፡፡
- የሃይማኖት ማስተማርያ ቴክስት ቡክ፡፡ ይህንን እንዲያዘጋጁ የተመደቡት የታክስ ፎርሱ አባላት፤ አቶ ዳንኤል፤ አቶ የሻነው እና አቶ ሰሎሎሞን ናቸው፡፡
3. የአዳጊዎች መዘምራን በተመለከተ
- በትምህርት ክፍሉ የታቀፉት ከ150 በላይ የሚሆኑ አዳጊ ልጆች፤ በየሳምንቱ እሁድ ከቅደሴ በኋላ መዝሙር የመያቀርቡበት መርሐ ግብር ተነድፏል፡፡ ይህንን ለማድረግ፤ ልጆቹ በየክፍላቸው የሚያጠኑት መዝሙር እና የሚያቀርቡ መዝሙር ዝርዝር እቅድ ተዘጋጅቶ፤ በቅርቡ በዚህ ድረ ገጽ ላይ ይለጠፋል፡፡
- ተማሪዎች፤ ወላጆች እና መምህራን የሚተዋወቁበት እና የሚመካከሩበት አጋጣሚዎችን ማብዛት አስፈላጊ መሆኑ ስለታመነበት፤ በሚቀጥሉት ወራት ውስጥ የቤተሰብ በዓል ቀን ተወስኖ፤ ልጆች ከወላጆቻው ጋር የሚታደሙበት፤ እየተዝናኑ የሚመካከሩበት መርሐግብር ይዘጋጃል፡፡ ይህም መርሐግብር በአቶ ቢኒያም እና በአቶ መሠረት አስተባባሪነት ይከናወናል፡፡
6. የዓምደ ሃይማኖት ክፍል የመማር ማስተማር ሂደት ያሉበትን ውስብስብ ችግሮች በተመለከተ ጥልቅ ውይይይት ተደርጎባቸዋል፡፡
No comments:
Post a Comment
እናመሰግናለን፡፡ተሳትፎዎን ይቀጥሉ፡፡