
ፈተናው
የሚሰጠው በሁለት መንገድ ነው፡፡ የመጀመርያው መንገድ፤ ተማሪዎች እዚያው ክፍል ውስጥ የሚጨርሱት የክፍል ፈተና ነው፡፡ ሁለተኛው
መንገድ ደግሞ ተማሪዎች እቤት ወስደው ከወላጆቻቸው ጋር ይሚሰሩት፤ እቤት የሚወሰድ ፈተና ሲሆን ዓላማውም የወላጆችን ተሳትፎ ለመመዘን
ነው፡፡
የፈተናው
ይዘት፤ እንደ ተማሪዎቹ የክፍል ደረጃ ቢለያይም፤ ጥያቄዎቹ የሚያተኩሩት ግን በ ሁለት የትምርት ዘርፎች ላይ ይሆናል፡፡ 1ኛ. የአማርኛ
ቋንቋ ማለትም (ፊደል፤ ንባብ፤ ጽሑፍ፤ ንግግር) 2ኛ. የሃይማኖት ትምህርት ማለትም (እምነት፤ ሥርዓት እና መዝሙር)
እንደተለመደው፤
ፈተና የሚሰጠው የተማሪዎችን እውቀት ለመመዘን ቢሆንም፤ በደብሩ የሚሰጠው ፈተና ግን ከዚህ በላይ ተጨማሪ ግቦች አሉት እነርሱም፡
- በትምህርት ቤቱ፤ ወጥ የሆነ እና የተቀናጀ የፈተና እና የምርቃት ሥርዓት ባሕል መጀመር
- የሥርዓተ ትምህርቱን ውጤታማነት መገምገም
- ወላጆች በማስተማር ሂደት ውስጥ ያላቸውን ተሳትፎ መመዘን ነው፡፡
የፈተናው
ውጤት፤ ለተማሪዎቹ ወላጆች የሚላክ ሲሆን፤ የውጤት ማሳወቂያው የሚይዘው የተማሪዎቹን የፈተና ውጤት፤ የክፍል አቴንዳንስ እና የመምህራኑን
አስተያየት ነው፡፡ ናሙናውን ለማየት ይህንን ይጫኑ፡፡
this great thank you
ReplyDelete