Wednesday, January 2, 2013

የመዝሙር መማርያ መጽሔት ዝግጅት ተጀምሯል


አዳጊ ልጆች መዝሙራትን ማጥናት ብቻ ሳይሆን፤ ስለ ኦርቶዶክሳዊ መዝሙርም መሰረታዊ እውቀት እንዲኖራቸው የሚያደርግ የመዝሙር መማርያ መጽሔት ዝግጅት ተጀምሯል፡፡ ዝግጅቱ የሚመራው በሰንበት ትምህርትቤት ውስጥ በመዘምራንነት በምታገለግለው ዘማሪት ቀጸላ ነው፡፡
የመማርያ መጽሔቱ ይዘት የሚከተለውን እንዲመስል የታሰበ ሲሆን፤ ጽሑፉ በቤተክርስቲያን መምህራን ታርሞ ሲጸድቅ፤ ልጆቹ እንዲማሩበት የሚደረግ ይሆናል፡፡መጽሔቱ መግለጫ ስዕላትን የሚይዝ ሲሆን፤ በተቻለ መጠንም የእንግሊዝኛ ትርጉምም እንዲኖረው ይሞከራል፡



ይዘት
·         ኦርቶዶክሳዊ መዝሙር ምንድን ነው?
·         የቅዱስ ያሬድ ታሪክ
·         የመዝሙር መገልገያዎች
·         የተመረጡ መዝሙሮች
o   ለንባብ ክፍል
o   ለመሠረተ ሃይማኖት ክፍል
o   ለዓምደ ሃይማኖት ክፍል
·         ጥያቄ እና  መልሶች

መጽሔቱ በጃንዋሪ 2013 የሚጀመር ሲሆን በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ እንዲጠናቀቅ ይጠበቃል፡፡

No comments:

Post a Comment

እናመሰግናለን፡፡ተሳትፎዎን ይቀጥሉ፡፡

blessing

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን፡፡.......In The Name of The Father, The Son and The Holy Spirit. Amen.

Amen

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ ወለ ወላዲቱ ድንግል፤ ወለ መስቀሉ ክቡር፤ አሜን::