Monday, January 14, 2013

የሳምንቱ ክንውኖች እና ተስፋዎች

ዛሬ እሁድ ጃንዋሪ 13 2013፤ በአዳጊዎች ትምህርት አገልግሎት ክፍል የተጠናቀቁ፤ የተጀመሩ እና ተስፋ የተገኘባቸው አያሌ ነገሮች ተከናውነዋል፡፡

1ኛ. ተማሪዎች ተመርቀዋል፡፡ የአለፈው ዓመት፤ በመምህር ካሰኝ ማብረጃ እና በመምህር የሻነው መኮንን ፤ የአማርኛ ቋንቋ እና የሃይማኖት ትምህርት ተከታትለው ያጠናቀቁ ተማሪዎች በአባቶች ቡራኬ እና ጸሎት ተመርቀዋል፡፡



የመርሃግብሩን ዝርዝር ሪፖርት እና ፎቶግራፎችን ለማየት፤ የመሠረተ ሃይማኖት ክፍልን ገጽ ይህን ሊንክ በመጫን ያንብቡ›››
2ኛ. የጀማሪ ተማሪዎች ክፍል ተከፍቷል፡፡ ይህ አዲስ ክፍል የተከፈተው፤ በጊዜያዊነት፤ በቤተክርስቲያኑ አዳራሽ መድረክ ላይ ሲሆን፤ የማስተማርያ መንገዱም በኦቨር ሄድ ፕሮጀክተር ነው፡፡ ክፍሉን በዋና አስተባባሪነት የሚመሩት መምህር  ሲሳይ ግዛቸው ነው፡፡
በኦቨር ሄድ ፕሮጀክተር ፊደል ሲታይ (ካሜራዬ ሰነፍ ሆኖ እንጂ፤ ቤቱ ጨለማ አይደለም)
3ኛ. የመልካም ልደት ካርድ መላክ ተጀመሯል፡፡ በዚህ ጃንዋሪ ወር ውስት፤ ልደታቸውን ለሚያከብሩ ተማሪዎቻችንን፤ የመምህራን ፊርማ ያለበት የቤተክርስቲያን ፖስት ካርድ በቤት አድራሻቸው ተልኮላቸዋል፡፡ ይህም የፖስታ መልዕክት አገልግሎት፤ ወደፊት፤ ፖስት ካርድ ከመላክ አልፎ ወላጆች በየቤታቸው ለልጆቻቸው የሚሆኑ ትምህርቶችን የሚያገኙበትም መንገድ እንደሚሆን ተስፋ ይደረጋል፡፡
4ኛ. ጠቃሚ ፕሮፌሽን ያላቸው ወላጆች አገልግሎቱን ተቀላቅለዋል፡፡ ይህም ትልቅ ተስፋ ነው፡፡ ከእነዚህም ውስጥ አርቲስት ወ/ሮ ፍቱን ለአዳጊዎች ለሚዘጋጁ መጽሔቶች እና መጽሐፍት ኢሉስትሬሽን ስዕሎች ለማዘጋጀት ፈቃደኝነታቸውን ገልጸው የመጽሔት ዝግጅት ፕሮጀክት ተቀብለዋል፡፡ በአማርኛ ታይፒንግ እና በማስተማር ሊረዱ የሚችሉ ፈቃደኛ ወላጆች (ወ/ሮ ሰናይት ጣሰው እና ወ/ሮ እናትዓለም)፤ እንዲሁም አዳጊዎቹን መዝሙር በማስጠናት እና የመዝሙር መማርያ መጽሔት በማዘጋጀት የሚረዱ ሰንበት ተማሪዎች (ዘማሪት መታሰቢያ ካሳ እና ዘማሪት ትርንጎ አበበ ፈቃደኝታቸውን ገልጸዋል፡፡

No comments:

Post a Comment

እናመሰግናለን፡፡ተሳትፎዎን ይቀጥሉ፡፡

blessing

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን፡፡.......In The Name of The Father, The Son and The Holy Spirit. Amen.

Amen

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ ወለ ወላዲቱ ድንግል፤ ወለ መስቀሉ ክቡር፤ አሜን::