Sunday, June 30, 2013
የፊደል ቤት የ2013 ሁለተኛ ሩብ አመት ፈተና
የፊደል ቤት የ2013 ሁለተኛ ሩብ አመት ፈተና በ ጁን 30, 2013 እና በ ጁላይ 7, 2013 ይሰጣል፡፡ የፈተናውን ይዘት ለመመልከት ይህንን ይጫኑ፡፡
Tuesday, June 25, 2013
የመዝሙር ጥናት መርሐግብር
አዳጊ ልጆች ኦርቶዶክሳዊ መዝሙራትን የሚያጠኑበት፤ ከቤተክርስቲያን የመዝሙር መሳሪያዎች፤ ሥርዓት እና ባህል ጋር
የሚተዋወቁበት የትምህርት መርሐ ግብር ተዘጋጅቶላቸዋል፡፡ የአራቱ ክፍል ተማሪዎች፤ በየሳምንቱ፤ በተራ በተራ፤ በቤተክርስቲያን ውስጥ
ለምዕመናን መዝሙር እንዲያቀርቡ ማስቻል የመርሐግብሩ ተጨማሪ ግብ ነው፡፡

የመዝሙር ጥናት ወርኃዊ መርሐግብር፤ በዚህ ድረ ገጽ ላይ በተዘጋጀው የመዝሙር መርሐግብር ገጽ() ላይ ይለጠፋል፡፡ እንደ አስፈላጊነቱም፤ ሙሉ የመዝሙራት ስንኞች ይለጠፋሉ፡፡
Sunday, June 23, 2013
በኪነ ጥበቡ አየለ
ይህ ድንቅ ልጅ የሚሰራቸውን የእደ ጥበብ ውጤቶች የሚያይ ሰው በሁለት ነገር ይገረማል፤ 1ኛ. ልጁ
በሚሰራቸው የእደ ጥበብ ስራዎች ጥራት 2ኛ. በልጁ የመጠሪያ ስም እና ግብር መጣጣም፡፡
ስሙ በኪነ ጥበቡ አየለ ይባላል፡፡ በደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርርስቲያን የመሠረተ ሃይማኖት
ክፍል ተማሪ ነው፡፡ በኪነ ጥበቡ ካለው ጨዋ ስነምግባር እና የቤተክርስቲያን ፍቅር በተጨማሪ፤ ኢትዬጵያዊ ባሕሉን እና ታሪኩን የሚያንጸባርቁ
የእደ ጥበብ ስራዎችን ይሰራል፡፡
![]() |
በኪነጥበቡ አየለ ከጥበብ ሥራዎቹ ጋር |
![]() |
በኪነጥበቡ አየለ እና ዘማሪ የሻነው መኮንን |
በፎቶግራፉ ላይ እንደምታዩት፤ የሰራው ሞዴል፤ ‹‹የልጅ ሥራ›› አይመስልም፡፡ በቅርጹ ተመጣጣኝነት፤ በክሮቹ አደራደር እና አቆጣጠር ረቂቅነት፤ በሞዴሉ ጥንካሬ እና ሞዴሉን ለመስራት በተጠቀመባቸው ጥሬ እቃዎች እንደሚንጻባረቀው፤ የኪነጥበቡ ሥራ የጥበበኛ ሥራ ነው፡፡
የኪነ
ጥበቡን ሥራዎችን መነሻ በማድረግ፤ የደብሩ አዳጊዎች ክፍል፤ ወደፊት፤ በአዳጊዎች የተሰሩ ተመሳሳይ የእደ ጥበብ እና ፈጠራ ውጤቶችን ለምዕመናን የሚያሳይበት፤
ለሌሎች ልጆችም ማስተማርያ የሚያውልበት መላ እንደሚፈልግ ይጠበቃል፡፡
Monday, June 17, 2013
የመምህራን እና አስተባባሪዎች ጠቅላላ ውይይት
የአዳጊዎች ትምህርት ክፍል መምህራን እና አስተባባሪዎች፤ እሁድ ጁን 16 2013 ጠቅላላ ውይይት አድርገው ነበር፡፡ በውይይቱም የተሳተፉት አባላት ብዛት 12 ሲሆኑ፤ የተወያዩበት እና ያስተላለፉትም ውሳኔዎች ከሞላ ጎደል ይህንን የመስላሉ፡፡
1. የተዘጋጀውን ካሪኩለም ከልጆቹ አቅም/ ደረጃ/ ጋር ማጣጣምን በተመለከተ፡፡
በየክፍሉ ያሉ ተማሪዎች የቋንቋ እውቀት እና የእድሜ ደረጃ የተዘበራረቀ ስለሆነ፤ የተዘጋጀውን ካሪኩለም ለመተግበር እንቅፋት ሆኗል፡፡ ህይንን ለማስተካከል ሁለት ደረጃዎቸ ያሉት መፍትሔ ታስቧል፡፡
የአዳጊዎች ትምህርት ክፍል ተማሪዎች የሚማሩበት፤ መምህራንም የሚያስተምሩበት ቋሚ ማስተማርያ መጽሐፍ/ ቴክስት ቡክ/ የለም፡፡ በሚቀጥለው የትምህርት ዘመን፤ የሚከተሉት ቴክስቶች እንዲዘጋጁ፤ ታስክ ፎርስ ተቋቁሟል፡፡
3. የአዳጊዎች መዘምራን በተመለከተ
6. የዓምደ ሃይማኖት ክፍል የመማር ማስተማር ሂደት ያሉበትን ውስብስብ ችግሮች በተመለከተ ጥልቅ ውይይይት ተደርጎባቸዋል፡፡
1. የተዘጋጀውን ካሪኩለም ከልጆቹ አቅም/ ደረጃ/ ጋር ማጣጣምን በተመለከተ፡፡
በየክፍሉ ያሉ ተማሪዎች የቋንቋ እውቀት እና የእድሜ ደረጃ የተዘበራረቀ ስለሆነ፤ የተዘጋጀውን ካሪኩለም ለመተግበር እንቅፋት ሆኗል፡፡ ህይንን ለማስተካከል ሁለት ደረጃዎቸ ያሉት መፍትሔ ታስቧል፡፡
- ደረጃ አንድ፡፡ የሁለተኛው ሩብ ዓመት ፈተና ከተሰጠ በኋላ፤ ለፊደል ቤት፤ ንባብ ቤት ፤ እና መሠረተ ሃይማኖት ተማሪዎች አዲስ አይነት የክፍል ድልድል ማድረግ፡፡ይህም በተማሪዎች የቋንቋ እውቀት ላይ የተመሰረተ ድልድል ስለሚሆን፤ በአንድ ክፍል ውስጥ ተመጣጣች ችሎታ/ደረጃ/ ያላቸውን ልጆች ለማግኘት ይረዳል፡፡ ወላጆች ይህንን አስቀድመው እንዲያውቁትም ማስታወቂያ ደብዳቤ ተልኳል፡፡
- ደረጃ ሁለት፡፡ በዓመቱ መጨረሻ ላይ፤ ካሪኩለሙ ለተማሪዎች ይመጥናል አይመጥንም የሚል ምዘና አድርጎ፤ የካሪኩለም ክለሳ ማካሄድ
የአዳጊዎች ትምህርት ክፍል ተማሪዎች የሚማሩበት፤ መምህራንም የሚያስተምሩበት ቋሚ ማስተማርያ መጽሐፍ/ ቴክስት ቡክ/ የለም፡፡ በሚቀጥለው የትምህርት ዘመን፤ የሚከተሉት ቴክስቶች እንዲዘጋጁ፤ ታስክ ፎርስ ተቋቁሟል፡፡
- ቋንቋ ማስተማርያ ቴክስተ ቡክ፡፡ ይህንን እንዲያዘጋጁ የተመደቡት የታክስ ፎርሱ አባላት አቶ መኮንን፤ አቶ ካሰኝ፤ አቶ ናዖድ እና ወ/ሮ እመቤት ናቸው፡፡
- የሃይማኖት ማስተማርያ ቴክስት ቡክ፡፡ ይህንን እንዲያዘጋጁ የተመደቡት የታክስ ፎርሱ አባላት፤ አቶ ዳንኤል፤ አቶ የሻነው እና አቶ ሰሎሎሞን ናቸው፡፡
3. የአዳጊዎች መዘምራን በተመለከተ
- በትምህርት ክፍሉ የታቀፉት ከ150 በላይ የሚሆኑ አዳጊ ልጆች፤ በየሳምንቱ እሁድ ከቅደሴ በኋላ መዝሙር የመያቀርቡበት መርሐ ግብር ተነድፏል፡፡ ይህንን ለማድረግ፤ ልጆቹ በየክፍላቸው የሚያጠኑት መዝሙር እና የሚያቀርቡ መዝሙር ዝርዝር እቅድ ተዘጋጅቶ፤ በቅርቡ በዚህ ድረ ገጽ ላይ ይለጠፋል፡፡
- ተማሪዎች፤ ወላጆች እና መምህራን የሚተዋወቁበት እና የሚመካከሩበት አጋጣሚዎችን ማብዛት አስፈላጊ መሆኑ ስለታመነበት፤ በሚቀጥሉት ወራት ውስጥ የቤተሰብ በዓል ቀን ተወስኖ፤ ልጆች ከወላጆቻው ጋር የሚታደሙበት፤ እየተዝናኑ የሚመካከሩበት መርሐግብር ይዘጋጃል፡፡ ይህም መርሐግብር በአቶ ቢኒያም እና በአቶ መሠረት አስተባባሪነት ይከናወናል፡፡
6. የዓምደ ሃይማኖት ክፍል የመማር ማስተማር ሂደት ያሉበትን ውስብስብ ችግሮች በተመለከተ ጥልቅ ውይይይት ተደርጎባቸዋል፡፡
Subscribe to:
Posts (Atom)