የወላጆች ጥረት በቤተክርስቲያን ተቋማዊ ዝግጅት ካልተደገፈ፤ በአንጻሩም የቤተክርስቲያን ዝግጅት በወላጀቾች መንፈሳዊ እና ቤተሰባዊ ጥረት ካልታገዘ፤ ልጆቻችን የያዙትን ይለቃሉ፤ ሲከፋም ስደተኞችን ለሚያጠቃው የማንነት ቀውስ አደጋ ይጋለጣሉ...ወዘተ እያልኩ ስለ ስለቤተክርስቲያን ተቋማዊ ዝግጅት በድጋሚ እንዳስብ ያደረገኝ ይሄ ልጅ ነው፡፡
ቀኑ ቃና ዘገሊላ ነውና፤ Jan 20, 2013፤ ውጪ፤ በቤተክርስቲያኑ ዓውደ ምህረት ላይ፤ ታቦተ ህጉ እየነገሰ ነው፡፡ ካህናትም ያሬዳዊ ዜማ እና ሽብሸባ እያቀረቡ ነው፡፡ ይሄ ልጅ ደግሞ