Monday, December 24, 2012

የምጥን መዝገበ ቃላት ዝግጅት ተጀመረ

በትምህርት ቤቱ የሚማሩ አዳጊ ተማሪዎች ከሃይማኖታዊ ትምህርቶች በተጨማሪ የአማርኛ ቋንቋም ይማራሉ፡፡ የቋንቋ መምህራኑ፤ የልጆቹን የቃላት እውቀት ለማዳበር የሚረዳ መዝገበ ምጥን መዝገበ ቃላት ማዘጋጀት ጀምረዋል፡፡ ሁሉም የቋንቋ መምህራን፤ ለተማሪዎቻቸው የሚመጥኑ ቃላትን ማዘጋጀት ጀምረዋል፡፡

መዝገበ ቃላቱ 365 ቃላትን እንዲይዝ የታሰበ ሲሆን፤ ዓላማውም ተማሪዎች በቀን አንድ ቃል፤ በዓመት ደግሞ 365 ቃላት እንዲያውቁ ማድረግ ነው፡፡ መዝገበ ቃላቱ ሲጠናቀቅ፤ የመዝገበ ቃላቱም ይዘት (ፎርማት)ም ይሄንን ይመስላል፡፡

ምሳሌ

ቤተክርስቲያን                                                            
Betekristian....................................Picture of a Church [here]
Church

እኔ ቤተክርስቲያን መሄድ እወዳለሁ
          Ene Betekirstian Mehed Ewedalehu
I like to go to church.

ፕሮጀክቱን በሦስት ወር (ጃንዋሪ፤ፌብሩዋሪ፤ማርች) ተሰርቶ የሚጠናቀቅ ሲሆን፤ መምህርት እታፈራሁ ሰሎሞን ፕሮጀክቱን ለማስተባበር እና ለማጠናቀቅ ኃላፊነት ተቀብለዋል፡፡

No comments:

Post a Comment

እናመሰግናለን፡፡ተሳትፎዎን ይቀጥሉ፡፡

blessing

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን፡፡.......In The Name of The Father, The Son and The Holy Spirit. Amen.

Amen

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ ወለ ወላዲቱ ድንግል፤ ወለ መስቀሉ ክቡር፤ አሜን::