Thursday, February 27, 2014

ከአንድ-ለሁሉም ወደ አንድ-ለአራት (የፊደል ቤት ተማሪዎች አዲስ የክፍል ሥርዓት)




የፊደል ቤት ተማሪዎች በአብዛኛው እድሜያቸው ከ5-7 የሚደርሱ ልጆች ሲሆኑ፤ በክፍል ውስጥም የሚማሩት ፊደል መቁጠር እና መጻፍ መለማመድ ነው፡፡ በሃይማኖትም ክፍለ ጊዜ ቀላል መዝሙሮችን ያጠናሉ፤ የቤተክርስቲያን ስዕላትን መለየት ይማራሉ፡፡ የተማሪዎቹ ቁጥር 20ም ይሁን 30፤ ትምህርቱ የሚሰጣቸው በአንድ መምህር ነበር (አንድ-ለሁሉም)፡፡


የአንድ-ለሁሉም የትምህርት አሰጣጥ ጠቃሚ የሚሆንበት ሁኔታዎች ቢኖሩም፤ የወላጆችን በትምህርት አሰጣጥ ውስጥ በብዛት ለማሳተፍ፤ ተማሪዎችንም በቅርብ ለመከታተል በቂ መድረክ አይሰጥም፡፡ በሁለተኛውም የመምህራን እና የወላጆች ጉባዔም ወቅት እንደተገለጸው፤ ከፌብሩዋሪ 2014 ጀምሮ የጀማሪ ክፍል የትምህርተ አሰጣጥ አንድ-ለአራት እንዲሆን ተደርጓል፡፡


የአንድ-ለአራት የትምህርት አሰጣጥ በአጭሩ፡- አንድ መምህር በክብ ጠረጴዛ ላይ በአማካይ 4 ተማሪዎችን ያስተምራል፡፡ በክፍል ውስጥ 28 ተማሪዎች ቢኖሩ፤ 7 ክብ ጠረጴዛዎች ይኖራሉ፤ 7 መምህራንም ይኖራሉ፡፡ ተማሪዎቹን የሚደለድሉት መምህራኑ ሲሆኑ፤ በየጠረጴዛው በመምህርነት የሚመደቡ ደግሞ የልጆች ወላጆች ናቸው፡፡ የዕለቱ ትምህርት የሚዘጋጀው እና የሚባዛው በመደበኛ የክፍሉ መምህራን ነው፡፡

በዚህ መሰረት፤ በአሁኑ ሰዓት ያለው የተማሪዎች ምደባ እና የወላጅ መምህራን ዝርዝር ከዚህ በታች ባለው ሰንጠረዥ ተመልክቷል፡፡ ይህ ዝርዝር፤ በመምህራኑ እና በወላጅ መምህራን ግምገማ መሰረት በየወቅቱ ሊለወጥ ይችላል፡፡
 
ዋና መምህራን

1.      ሐና ደጋ…ፊደል አስተማሪ

2.     ሰሎሞን ኪዳኔ…..ግብረ ገብ አስተማሪ
 

 
ምድብ
የተማሪ ሥም
ወላጅ መምህራን
 
1
አብኬም በረከት 
ቤተልሄም ተመስገን
ሊያ ቢንያም
ኤደን ፈለቀ
ሰብለ/ሕይወት
 
 
2
ህዝቅኤል ሰለሞን
ማራኪ ግዛው
አቢጌል ታሪኩ
ፌቨን እስክንድር
ቤዛ/ኢየሩ
 
3
በረከት ዋለልኝ
ፍቅር ሠይፈ
ቤተል አይምሮ
አቤኔዘር ታዬ
ዓብይ/ገነት
 
4
ኤልዳ ሙሉጌታ
ኤደን መሰረት
ፀጋ ታፈሰ
ሄይመን አሌክስ
ሶፍያ/አልማዝ
 
5
ልደት አርጋው
ሃና አክሊል
ሊዲያ መስፍን
ሜሪ ሰለሞን
መሰረት
 
6
ሙሴ ተድላ
ረድኤት መስፍን
ረድኤት ዋለልኝ
ሶሊያና ሙሉጌታ
ሙላት
 
7
ናቲ አትክልቲ
ያሬድ ስንታየሁ
ካሌብ መሳፍንት
መፍትሄ ዳንኤል
ማቲ ኩዊን
አማኑኤል ተመስገን
ቤተልሔም አሰፋ
መለይ ፈቃደ
 
(ትልቅ ክብ ጠረጴዛ ላይ ያሉ)
8
ኖላዊ ግዛው
ኪሩቤል መስፍን
ዳዊት ፈለቀ
ናሆም መስፍን
ሐረገወይን
 

Monday, January 6, 2014

ሁለተኛው ዙር የወላጆች እና መምህራን ጉባዔ ውጤት

 
በትናንትናው ዕለት እሁድ ጃንዋሪ 5 ቀን 2014 የወላጆች እና መምህራን ጠቅላላ ጉባዔ ለሁለተኛ ጊዜ ተካሂዷል፡፡ የጉባዔው ዋና ዓላማ አዲሱን የልጆች ትምህርት ቤት መዋቅር እና አሰራር ለማሳወቅ እና ትምህርት ቤቱን የሚያስተዳድሩ በጎፈቃደኛ ኮሚቴዎችን ማስመረጥ ነበር፡፡

መርሐግብሩ የተጀመረው በቤተክርስቲያኑ ቦርድ ሊቀመንበር አቶ እስጢፋኖስ የመክፈቻ ንግግር ሲሆን፤ በንግግራቸውም ደብሩ ለአዳጊ ልጆች ትምህርት ቤት መጠናከር ያደረጋቸውን ጥረቶች እና በቅርቡ ለማድረግ የተዘጋጃቸውን ድጋፎች በአጭሩ ገልጸዋል፡፡ በገለጻቸውም

1.      ለትምህርት ቤቱ አስተባባሪ እና አስተማሪ የሚሆን ባለሙያ የመቅጠር ሥራ በቅርቡ እንደሚጀመር አሳውቀዋል

2.     ለትምህርትቤቱ እና ለተማሪዎች የሚያገለግሉ የመማርያ ቁሳቁስ (ወንበር እና ጠረጴዛ) ግዢ በቅርቡ እንዲከናወን አስታውቀዋል

3.     ደብሩ የልጆች ትምህርት ቤት የሚያደርገውን በጎ ጥረት ሁሉ የመደገፍ ጥረታቸውን እንደሚቀጥሉ አሳውቀዋል

ሁለተኛው መርሐግብር ለታዳሚዎች ስለ ትምህርትቤቱ ይዘት፤ ሥራዎችን እና ስለ ስብሰባው ዋና ዓላማ መግለጽ ነበር፡፡ ገለጻውን ያደረጉት የወቅቱ የአዳጊ ልጆች ትምህርትቤት ሰብሳቢ ወ/ሮ እመቤት አካሉ ሲሆኑ በገለጻቸውም

1.      ትምህርትቤቱ ቢያንስ 189 አዳጊ ልጆችን መዝግቦ እንደሚያስተምር

2.     ትምህርትቤቱ የተጠና ሥርዓተትምህርት እንዳለው

3.     ትምህርትቤቱ የራሱ ድረ ገጽ እንዳለው

4.     ወላጆችን የሚያሳትፍ እና የትምህርቱን ጥራት የሚጨምር አዲስ የአስተዳደር መዋቅር መዘጋጀቱን

5.     ትምህርትቤቱ ከደብሩ ቦርድ በቂ እና ቅን ድጋፍ እያገኘ እንደሆነ

6.     የዛሬው ስብሰባ ዓላማም በጎፈቃደኛ ወላጆች የሚያገለግሉበትን ዘርፍ እንዲመርጡ ማበረታታት እና አዲስ የትምህርት ቤት አስተዳደር ኮሚቴ ማስመረጥ እንደሆነ ገልጸዋል

ሦስተኛው መርሐግብር ስለ አዲሱ የትምህርት ቤቱ የአስተዳደር እና አደረጃጀት መዋቅር ማብራሪያ መስጠት እና ኮሚቴዎችን ማስመረጥ ነበር፡፡ ይህንን መርሐግብር የመሩት አቶ ናዖድ ቤተሥላሴ ሲሆኑ፤ በመርሐግብሩም ላይ

1.      የአዲሱን መዋቅር አስፈላጊነት፤ ይዘት እና አሰራር የተመለከተ ገለጻ አድርገዋል

2.     የትምህርት አሰጣጡ ወደ ክብ ጠረጴዛ ትምህርት እንደሚቀየር እና በክፍል ቢያንስ 5 ወላጅ መምህራን እንደሚያስፈልጉ

3.     ወላጆች ማገልገል የሚፈልጉበትን ክፍል ወይም ንዑስ ክፍል እንዲመርጡ እድል ሰጥተዋል

4.     በመጨረሻም በኮሚቴነት ማገልገል የሚፈልጉ ወላጆች ራሳቸውን እንዲጠቁሙ እድል ሰጥተው በጎፈቃደኞችን አስመርጠዋል

በመርሐግብሩ መጨረሻም ተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎችን ያቀረቡ ሲሆን ከጥያቄዎቹም ውስጥ

1.      ስለሚቀጠረው መምህር አቀጣጠር እና መመዘኛዎች ምንነት ማብራሪያ ተጠይቋል

2.     ትምህርትቤቱ ቲነጀሮችን በመርዳት ዙርያ ለማድረግ ስላሰበው ጥረት አስተያየት እና ጥያቄ ተሰጥቷል

3.     ስለሚጀመረው የቱተር አገልግሎት አሰራር ማብራሪያ ተጠይቋል

4.     ተጀምሮ የተቋረጠው የጀማሪ ተማሪዎች ክፍል መቼ እንደሚጀመር ጥያቄ ተጠይቋል

5.     የማስተማርያ ቋንቋንም በተመለከተ አስተያየቶች ተሰጥተዋል

በመርሐግብሩ መጨረሻም ወላጆች ለአገልግሎት የመረጧቸውን ክፍሎች በተሰጣቸው ወረቀት ላይ አስፍረው የመለሱ ሲሆን፤ በውጤቱም 49 ወላጆቸ የመጀመርያ፤ ሁለተኛ እና ሦስተኛ የአገልግሎት ምርጫቸውን አሳውቀዋል፡፡ በሚቀጥሉት ሳምንታትም፤ በኮሚቴነት ለማገልገል ፈቃደኝነታቸውን የገለጹ ወላጆች ተሰባስበው፤ ዋና አስተባባሪያቸውን ይመርጣሉ፡፡ ሙሉ ዝርዝሩንም ለቦርድ ያሳውቃሉ፡፡
 

Thursday, December 5, 2013

ወላጆች ስለ ትምህርትቤታችን ምን ይላሉ?

ኖቬምበር 3 2013 በተጠራው የወላጆች እና መምህራንን የምክክር ስብሰባ ላይ 41 ወላጆች እና መምህራን እንዲሁም የደብሩ አስተዳደር ተገኝተው ነበር፡፡ በዕለቱ በአዳጊዎች ትምህርት ቤቱ እንቅስቃሴዎች፤ ጥንካሬዎች እና ድክመቶች ውይይት ተደርጓል፡፡

ከውይይቱ በተጨማሪ ግን ወላጆች ስማቸውን ሳይገልጹ እንዲመልሱት የተዘጋጀ መጠይቅ ተሰጥቷቸው ነበር፡፡ መጠይቁ 17 ጥያቄዎች ያሉት ሲሆን የጥያቄዎቹም ይዘት በተማሪ ልጆች፤ በመምህራን፤ በወላጆች ጥረት፤ በትምህርት ቤቱ የወደፊት ተስፋ፤ እና የገንዘብ ክፍያን ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ነበሩ፡፡ (የታደለውን መጠይቅ ለማየት ይህንን ይጫኑ)

ወላጆች በመጠይቁ ወረቀት ላይ ያሰፈሩት መልሶች ሲጠቃለሉ በአብዛኛው በጎ እና ደጋፊ አመለካከት እንዳላቸው ሲያመለክት፤ አሉታዊ መልስ የሰጡባቸው ጥያቄዎች ለወደፊቱ በትምህርት ቤቱ ጥራት ላይ ማሻሻያ ለማድረግ የሚረዱ ጥቆማዎች ሆነው ተገኝተዋል፡፡ (የተጠናቀረውን የወላጆችመልስ እና ውጤት ለማየት ይህንን ይጫኑ)፡፡  ውጤቱም ለወላጆች በቤት አድራሻቸው ተልኳል፡፡

Sunday, December 1, 2013

የልምድ ልውውጥ ሪፖርት

በናዖድ ቤተሥላሴ
በደብራችን በደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን (3010 Earl Pl NE Washington, DC 20018) የሚገኘውንም የአዳጊዎች ትምህርት ክፍል ለማጠናከር እየተደረጉ ካሉ ዘርፈ ብዙ እንቅስቃሴዎች ውስጥ አንዱ የሌሎች እህት አብያተ ክርስቲያናትን ልምድ እና አሰራር ልምድ መቅሰም ነው፡፡
 
እሁድ ዲሴምበር 02 2013 በደብረ ገነት መድኃኒአለም ቤተክርስቲያን (4401 Old Branch Avenue  Temple Hills, MD 20748) ተገኝቼ፤ የአዳጊ ልጆች እና ወጣቶች ትምህርት አሰጣጥን ለመጎብኘት፤ ከልምዳቸውም ብዙ ለመማር ችያለሁ፡፡ ያገኘሁትንም መሰረታዊ ትምህርት፤ ጠቃሚ ልምድ እና ምክር በአጭሩ እነሆ፡-

·         ትምህርት ቤቱ፡- መስራታቸው በግልጽ የሚታይ  የቦርድ ተወካይ፤ የሃይማኖት መምህር እና የትምህረት ኮሚቴዎች አሉት

o   ለልጆች ትምህርት ቤት ብቻ የሚውል ብዙ ክፍሎች ያሉ አንድ ሙሉ ቤት ገዝተዋል

o   በደብሩ የታወቀ እና የተፈቀደ በፈንድ ሬዚንግ አድርገው በተለያየ ጊዜ 30 ሺ እና 40 ሺ ዶላር አሰባስበዋል

o   በደብሩ ሥር ያለ፤ የታወቀ የባንክ አካውንት አለው

o   የተጻፈ መተዳደሪያ ደንብ፤ የተሳለ አስተዳደራዊ መዋቅር፤ በቂ የማስተማርያ ቦታ አለው

o   በቋሚነት፤ ለልጆች ትምህርት ቤት የተቀጠረ የሃይማኖት መምህር (ካህን) አለው

o   እስከ 200 የሚደርሱ መደበኛ ተማሪዎች አሉ

o   የተጻፈ የቋንቋ ካሪኩለም/ሳምንታዊ ትምህርቶች/ አሉት

o   36 ቋሚ ነገር ግን በጎፈቃደኛ መምህራን አሉት

o   ወላጆች ተራ ወጥቶላቸው በየሳምንቱ መምህራንን ወይም ልጆቹን ይረዳሉ

o   የአካዳሚ ቱተር አገልግሎት ይሰጣል

o   ለውጤታማ ተማሪዎች ስኮላርሺፕ ይሰጣል

·         ተማሪዎች

o   ሦስት ምድብ አላቸው

§  ዕድሜ 5-7(ጀማሪ ደረጃ)     --ዕድሜ 8-12(መካከለኛ ደረጃ)  --ዕድሜ 13-18(የመጨረሻ ደረጃ)

o   የትምህርት ሰዓታቸው 7፡45-11፡00 ነው

o   በወር አንድ እሁድ ቅዳሴ እንዲያስቀድሱ ይደረጋል

o   የሚማሩት አማርኛ ቋንቋ፤ ሃይማኖት፤ እና ግብረ ዲቁና ነው

o   ዓመታዊ የምርቃት እና የጌት ቱጌዘር ዝግጅቶች አላቸው

·         መምህራን

o   በአንድ ክፍል 5 መምህራን ያስተምራሉ

o   አንድ መምህር አንድ ክብ ጠረጴዛ ይይዛል፤ በዕለቱ፤ በየጠረጴዛው በአማካይ ከ4-5 ተማሪዎች አይቻለሁ፡፡

o   በዕለቱ የሚያስተምሩት ትምህርት; በትምህረት ክፍሉ ተዘጋጅቶ ይሰጣቸዋል

o   የክፍል ፈተና ያርማሉ፤ ፈተና ይሰጣሉ፤

o   በቀጥታ ከወላጆች ጋር አይደራደሩም፡፡ የወላጆችን ኮሚቴ የወላጆችን  ጉዳይ ይይዝላቸዋል፡፡

·         የተማሪ ወላጆች

o   የደብሩ አባል መሆን አለባቸው

o   ክፍያ ይከፍላሉ (ለስናክ፤ ለአልባሳት፤ ለስቴሽነሪ የሚሆን)

§  በቤተሰብ፡- ለ1 ልጅ 10 ዶላር፤ ለ2 ልጅ 15 ዶላር፤ ለ3 ልጅ 20 ዶላር

o   የወላጆች አስተባባሪዎች አሉ

o   የወላጆች አለግልግሎት መመሪያ ማኑዋል ይሰጣቸዋል

o   ወላጆች በወር አንድ ጊዜ የሚያገለግሉበት መርሀግብር ይወጣላቸዋል

o   በስልክ፤ በኢሜይል፤ በአካል፤ በቤተክርስቲያን መድረክ ላይ ማሳሰቢያ እና ጥሪ ይደረግላቸዋል

o   በየሳምንቱ 15 ወላጆች (በየክፍሉ 5) ይመደባሉ

·         ኮሚቴዎች

o   ያነጋገርኳቸው አራት አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት ናቸው

o   ያየኃቸው ግልጽ የሥራ ኃላፊነትያላቸው እና እርስ በእርሳቸው ደስ የሚል መግባባት ያላቸው ናቸው፡፡

o   ነባር እና የአገልግሎቶ ዓላማቸውን የሚያውቁ ስለሆኑ የአገልግሎቱን ውስጥና ውጪ፤ ድክመት እና ጥንካሬ ለይተው ያውቃሉ

o   በዲያስፖራ ወላጆች ውስጥ ያለ የልጅ አስተዳደግ ፓራዶክዶክስ እና የልጆች ማንነት ቀውስ ችግር በጥልቅ የተረዱ ስለሆኑ የትምህርት ቤቱን እንቅስቃሴ ይህንን ማኅራዊ ችግር በመፍታት ዙርያ እንዲቃኝ እየሞከሩ ነው፡፡

o   የሰጡኝ አክብሮት፤ ትምህርት እና ምክር የማይረሳ ነው፡፡

·         የስኬት መላዎች

o   ከወላጆች ጋር አንድ- ለአንድ ግብብነት መፍጠር

o   ደንቦችን ወላጆች እንዲያረቁ መጋበዝ፤ ከዚያ ማስፈጸም፤ ማስከበር፤ መሞከር

o   አገልግሎቱን በተገኘው አጋጣሚ እና መንገድ ሁሉ ማስተዋወቅ

o   ልጆች ቤተክርስቲያን ውስጥ ችሎታቸውን የሚያሳዩበት መድረክ (መነባንብ፤ ድራማ ወዘተ..) መፍጠር

o   ስኮላር ሺፕ፤ ሽልማት... መፍጠር
Measure of Success
  • Because of the kids school, the number of Church members increased by 30%
  • 100% of the kids that have passed through the school system are now in college
  • Those college kids (especially those who won the church's scholarship) serve back their church in their field of profession and preference.
  • Above all, the school is a proud source of well mannered, socially stable and academically competent citizens for the community.

The committee (ዶ/ር ሶሎሞን ገብሩ: ቢኒያም ገብረወልድ: ሐና ተስፋዬ: ቤተልሔም ዘውዴ: ) express their willingness to continue sharing their experience and resources as needed.

Friday, September 20, 2013

እንቁጣጣሽ መዝሙር


የደብሩ አዳጊ ልጆች ለ2006ዓ.ም መቀበያ እንቁጣጣሽ መዝሙር ሲያቀርቡ


blessing

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን፡፡.......In The Name of The Father, The Son and The Holy Spirit. Amen.

Amen

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ ወለ ወላዲቱ ድንግል፤ ወለ መስቀሉ ክቡር፤ አሜን::