Sunday, May 4, 2014

አዲስ የትምህርት መጀመርያ ሰዓት


ማሳሰቢያ

 የአዳጊ ልጆች ትምህርት የሚጀመረው ከቁርባን በኋላ ነበር፡፡ አሁን ግን ልጆች ስለ ቁርባን ሥርዓት እና ስለ ሃይማኖታቸው በደንብ እንዲማሩ ለማድረግ ትምህርት የሚጀመርበትን ሰዓት ከቁርባን ሰዓት በፊት ከ8፡00 ጀምሮ አድርገነዋል፡፡ ስለዚህ ከሚቀጥለው ሳምንት እሁድ ጀምሮ፡-

1ኛ. ልጆች ወደ ቤተክርስቲያን ሲመጡ፤ በቀጥታ ወደ መማርያ ክፍላቸው ይገባሉ፡፡ የተመደቡ ካህናት እና ዘማርያንም የሃይማኖት እና ሥርዓት ትምህርት ያስተምራሉ፡፡

2ኛ. የቁርባን ሰዓት ሲደርስ፤ ተማሪዎች ተሰልፈው ወደ ስርዓተ ቁርባን ይሄዳሉ

3ኛ. ከቁርባን በኋላ ተመልሰው ወደ መማርያ ክፍላቸው ይገቡና ትምህርታቸውን ይቀጥላሉ፡፡

ይህ አዲስ የትምህርት ልጆች በሥርዓተ ቁርባን ጊዜ የሚፈጽሙትን ስህተት ለማስተካከል እና ተጨማሪ የሃይማኖት ትምህርት እንዲያገኙ ለማድረግ ነው፡፡

የአዳጊዎች ክፍል የትምህርት ክፍል

No comments:

Post a Comment

እናመሰግናለን፡፡ተሳትፎዎን ይቀጥሉ፡፡

blessing

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን፡፡.......In The Name of The Father, The Son and The Holy Spirit. Amen.

Amen

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ ወለ ወላዲቱ ድንግል፤ ወለ መስቀሉ ክቡር፤ አሜን::