Sunday, May 11, 2014

የልጆች መምህር ፍለጋ

የደብራችን የአዳጊ ልጆች ትምህርት ክፍል፤ የአማርኛ ፊደል ያጠናቀቁ ተማሪዎችን የአማርኛ ቃላት ግንባታ እና ንባብ የሚያስተምር መምህር ይፈልጋል፡፡ ለማስተማር እችላለሁ የሚል መምህር ወይም መምህራን የሚከተሉትን ነጥቦች ያካተተ መረጃ እንዲልኩልን እንጠይቃለን፡፡

ትምህርትቤቱ መምህር የሚፈልገው ለአንድ ክፍል ተማሪዎች ሲሆን ተማሪዎቹ የተማሪዎቹ በዛት 25 ይደርሳል፡፡ ክፍሉ በቂ መቀመጫዎች እና ኋይት ቦርድ አለው፡፡ በተጨማሪም ትምህርትቤቱ ሌሲዲ ፕሮጀክተር እና ኦቨር ሄድ ፕሮጀክተር ማቅረብ ይችላል፡፡ የአማርኛ ክፍለ ጊዜ የሚጀምረው ልጆቹ ከቁርባን ከተመለሱ በኋላ ማለትም 10 ኤ.ሜ የሚጀምር ሲሆን የሚያልቀው ደግሞ 11 ሰዓት ነው፡፡
የማመልከቻ ይዘት
·         ሙሉ ስም
·         ስልክ ወይም ኢ-ሜይል
·         የሚያስተምሩበትን ዋጋ መጠን
·         የሚያስተምሩበትን ዓመታዊ ካሪኩለም ወይም ቴክስት ቡክ
·         በዓመቱ መጨረሻ ተማሪዎቹ እንዲህ እንዲያደርጉ ወይም ይሄ ችሎታ እንዲኖራቸው አደርጋለሁ የሚል የግብ መግለጫ
·         ስኬታማ ለመሆን ከትምህርትቤቱ የሚፈልጉትን ድጋፍ ዝርዝር

አመልካቾች ከላይ ያሉትን ነጥቦችን ያካተተ ማመልከቻ (ፕሮፖዛል) በማዘጋጀት በኢ-ሜይል dmk12@comcast.net naodforkids@gmail.com መላክ ይችላሉ፡፡
 
አመልካቾች የሚያቀርቡትን ፕሮፖዛል ለቤተክርስቲያኑ አስተዳደር ቀርቦ ተቀባይነት ካላገኘ ቅጥር አይካሄድም፡፡

 

Sunday, May 4, 2014

አዲስ የትምህርት መጀመርያ ሰዓት


ማሳሰቢያ

 የአዳጊ ልጆች ትምህርት የሚጀመረው ከቁርባን በኋላ ነበር፡፡ አሁን ግን ልጆች ስለ ቁርባን ሥርዓት እና ስለ ሃይማኖታቸው በደንብ እንዲማሩ ለማድረግ ትምህርት የሚጀመርበትን ሰዓት ከቁርባን ሰዓት በፊት ከ8፡00 ጀምሮ አድርገነዋል፡፡ ስለዚህ ከሚቀጥለው ሳምንት እሁድ ጀምሮ፡-

1ኛ. ልጆች ወደ ቤተክርስቲያን ሲመጡ፤ በቀጥታ ወደ መማርያ ክፍላቸው ይገባሉ፡፡ የተመደቡ ካህናት እና ዘማርያንም የሃይማኖት እና ሥርዓት ትምህርት ያስተምራሉ፡፡

2ኛ. የቁርባን ሰዓት ሲደርስ፤ ተማሪዎች ተሰልፈው ወደ ስርዓተ ቁርባን ይሄዳሉ

3ኛ. ከቁርባን በኋላ ተመልሰው ወደ መማርያ ክፍላቸው ይገቡና ትምህርታቸውን ይቀጥላሉ፡፡

ይህ አዲስ የትምህርት ልጆች በሥርዓተ ቁርባን ጊዜ የሚፈጽሙትን ስህተት ለማስተካከል እና ተጨማሪ የሃይማኖት ትምህርት እንዲያገኙ ለማድረግ ነው፡፡

የአዳጊዎች ክፍል የትምህርት ክፍል

blessing

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን፡፡.......In The Name of The Father, The Son and The Holy Spirit. Amen.

Amen

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ ወለ ወላዲቱ ድንግል፤ ወለ መስቀሉ ክቡር፤ አሜን::