Thursday, February 27, 2014

ከአንድ-ለሁሉም ወደ አንድ-ለአራት (የፊደል ቤት ተማሪዎች አዲስ የክፍል ሥርዓት)




የፊደል ቤት ተማሪዎች በአብዛኛው እድሜያቸው ከ5-7 የሚደርሱ ልጆች ሲሆኑ፤ በክፍል ውስጥም የሚማሩት ፊደል መቁጠር እና መጻፍ መለማመድ ነው፡፡ በሃይማኖትም ክፍለ ጊዜ ቀላል መዝሙሮችን ያጠናሉ፤ የቤተክርስቲያን ስዕላትን መለየት ይማራሉ፡፡ የተማሪዎቹ ቁጥር 20ም ይሁን 30፤ ትምህርቱ የሚሰጣቸው በአንድ መምህር ነበር (አንድ-ለሁሉም)፡፡


የአንድ-ለሁሉም የትምህርት አሰጣጥ ጠቃሚ የሚሆንበት ሁኔታዎች ቢኖሩም፤ የወላጆችን በትምህርት አሰጣጥ ውስጥ በብዛት ለማሳተፍ፤ ተማሪዎችንም በቅርብ ለመከታተል በቂ መድረክ አይሰጥም፡፡ በሁለተኛውም የመምህራን እና የወላጆች ጉባዔም ወቅት እንደተገለጸው፤ ከፌብሩዋሪ 2014 ጀምሮ የጀማሪ ክፍል የትምህርተ አሰጣጥ አንድ-ለአራት እንዲሆን ተደርጓል፡፡


የአንድ-ለአራት የትምህርት አሰጣጥ በአጭሩ፡- አንድ መምህር በክብ ጠረጴዛ ላይ በአማካይ 4 ተማሪዎችን ያስተምራል፡፡ በክፍል ውስጥ 28 ተማሪዎች ቢኖሩ፤ 7 ክብ ጠረጴዛዎች ይኖራሉ፤ 7 መምህራንም ይኖራሉ፡፡ ተማሪዎቹን የሚደለድሉት መምህራኑ ሲሆኑ፤ በየጠረጴዛው በመምህርነት የሚመደቡ ደግሞ የልጆች ወላጆች ናቸው፡፡ የዕለቱ ትምህርት የሚዘጋጀው እና የሚባዛው በመደበኛ የክፍሉ መምህራን ነው፡፡

በዚህ መሰረት፤ በአሁኑ ሰዓት ያለው የተማሪዎች ምደባ እና የወላጅ መምህራን ዝርዝር ከዚህ በታች ባለው ሰንጠረዥ ተመልክቷል፡፡ ይህ ዝርዝር፤ በመምህራኑ እና በወላጅ መምህራን ግምገማ መሰረት በየወቅቱ ሊለወጥ ይችላል፡፡
 
ዋና መምህራን

1.      ሐና ደጋ…ፊደል አስተማሪ

2.     ሰሎሞን ኪዳኔ…..ግብረ ገብ አስተማሪ
 

 
ምድብ
የተማሪ ሥም
ወላጅ መምህራን
 
1
አብኬም በረከት 
ቤተልሄም ተመስገን
ሊያ ቢንያም
ኤደን ፈለቀ
ሰብለ/ሕይወት
 
 
2
ህዝቅኤል ሰለሞን
ማራኪ ግዛው
አቢጌል ታሪኩ
ፌቨን እስክንድር
ቤዛ/ኢየሩ
 
3
በረከት ዋለልኝ
ፍቅር ሠይፈ
ቤተል አይምሮ
አቤኔዘር ታዬ
ዓብይ/ገነት
 
4
ኤልዳ ሙሉጌታ
ኤደን መሰረት
ፀጋ ታፈሰ
ሄይመን አሌክስ
ሶፍያ/አልማዝ
 
5
ልደት አርጋው
ሃና አክሊል
ሊዲያ መስፍን
ሜሪ ሰለሞን
መሰረት
 
6
ሙሴ ተድላ
ረድኤት መስፍን
ረድኤት ዋለልኝ
ሶሊያና ሙሉጌታ
ሙላት
 
7
ናቲ አትክልቲ
ያሬድ ስንታየሁ
ካሌብ መሳፍንት
መፍትሄ ዳንኤል
ማቲ ኩዊን
አማኑኤል ተመስገን
ቤተልሔም አሰፋ
መለይ ፈቃደ
 
(ትልቅ ክብ ጠረጴዛ ላይ ያሉ)
8
ኖላዊ ግዛው
ኪሩቤል መስፍን
ዳዊት ፈለቀ
ናሆም መስፍን
ሐረገወይን
 

blessing

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን፡፡.......In The Name of The Father, The Son and The Holy Spirit. Amen.

Amen

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ ወለ ወላዲቱ ድንግል፤ ወለ መስቀሉ ክቡር፤ አሜን::